Monday, December 8, 2014

“አሕመድ ያ ሐቢቢ”



ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
-------
አንዳንዶች “ነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) ትጠላላችሁ፤ በነቢዩ ላይ ሰለዋት አታወርዱም” ይሉናል፡፡ ሐቁ ግን የተገላቢጦሽ ነው፡፡ በነቢዩ ላይ ሰላምና ሰለዋት በማውረድ ከኛ የሚቀድም ማን ነው? እንዲያውም የነቢዩን ታላቅ ደረጃ በዜማ እየዘከርን እና ገድላቸውን እየተረክን ነው በርሳቸው ላይ ሰላምና ሰለዋት የምናወርደው:: ይህንን እውነታ ያስረዳልን ዘንድ የሱፊ ሼኾቻችን ትተውልን ያለፉትን አንድ “ነሺዳ” (የነቢዩ ውዳሴ”) እንጋብዛችሁ፡፡
  *****  *****  *****
    ነሺዳው መጠሪያ “አሕመድ ያ ሐቢቢ” ይሰኛል፡፡ “አሕመድ ወዳጄ ሆይ” እንደማለት ነው፡፡ እኛ ስናሰፋው “ አሕመድ የልቤ ወዳጅ”፤ “አሕመድ የነፍሴ ስር” ልንለው እንችላለን፡ (“አሕመድ” የነቢዩ ሙሐመድ -ሰ.ዐ.ወ- ሁለተኛ ስም ነው፡፡ ነቢዩ በመጨረሻው ቀን/የውመል ቂያማ የሚጠሩት አሕመድ በተሰኘው ስማቸው ነው)፡፡
    
   ይህንን “ነሺዳ” ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት በ1995 ዓ.ል. ይመስለኛል፡፡ ነሺዳውን በህብረት ሲዘምሩ የነበሩት መሰረቱን በኦምዱርማን ከተማ ባደረገውና “ፊርቀቱ-ሳሕዋ” በሚባለው ዝነኛ የሱዳን የነሺዳ ቡድን የታቀፉት ስድስት ወጣቶች ነበሩ፡፡ የቡድኑ አባላት የሚያዜሙት በአብዛኛው በታዋቂው ሼኽ ዐብዱረሒም አል-ቡረኢ የተጻፉትንና “መዲሕ” የሚባሉትን የነቢዩን ግጥማዊ መወድሶች በመሆኑ “አሕመድ ያ ሐቢቢ”ም የሼኽ አል-ቡረኢ ድርሰት ይመስለኝ ነበር፡፡ በ2001 ወደ ሀረር ከመጣሁ ወዲህ ግን “አሕመድ ያ ሐቢቢ” በአንድ ዘመንና በአንድ ስፍራ ያልተገደበ ውዳሴ እንደሆነ ለማወቅ ችያለሁ፡፡ ለዚህ ያበቃኝ ደግሞ በቀድሞ ዘመናት የተጻፈ አንድ “የመዲህ” ኪታብ (መጽሐፍ) በሀረር ለማየት መታደሌ ነው፡፡

     በርግጥም “የፊርቀቱ ሳሕዋ” ወጣቶች የሚዘምሩት “አሕመድ ያ ሐቢቢ” እና ከሀረር ያገኘሁት “አሕመድ ያ ሐቢቢ” አንድ መሰረት ያላቸው መሆኑን ከግጥሞቹ አሰካክ ለመረዳት ይቻላል፡፡ ሆኖም በመካከላቸው መጠነኛ ልዩነቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ ሱዳናዊያኑ ወጣቶች “አሕመድ ያ ሐቢቢ” በሚል ሐረግ የሚጀምረውን ባለሁለት መስመር ግጥም እንደ አዝማች አድርገው ይደጋግሙታል፡፡ የሀረሩ “አሕመድ ያ ሐቢቢ” ግን አዝማች የለውም፤ በዚህኛው ስልት “አሕመድ ያ ሐቢቢ” የሚለው ሐረግ አንድ ጊዜ ከታየ በኋላ አይደገምም፡፡ በሁለተኛ ደረጃም ሁለቱ የ“አሕመድ ያ ሐቢቢ” ስልቶች በግጥሞቻቸው ብዛት ይለያያሉ፡፡ የሀረሩ ስልት በኦምዱርማኑ ስልት ውስጥ የሌሉ ግጥሞቹ አሉት፡፡ በመሆኑም በግጥሞቹ ብዛት ከኦምዱርማኑ ስልት ይበልጣል፡፡
  
   የሀረሩ ስልት በትርፍነት ከያዛቸው ግጥሞች ውጪ ባሉት ግጥሞቹ ከኦምዱርማኑ ስልት ጋር የመመሳሰል ነገር ይታይበታል፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን በሁለቱ ስልቶች ያሉት ግጥሞች መቶ በመቶ የሚመሳሰሉበት ሁኔታ የለም፡፡ ግጥሞቹ አንዳንዴ በሁለት ስንኞቻቸው ብቻ ይመሳሰሉና በሶስተኛው ስንኝ ይለያያሉ፡፡ ሲያሻቸው ደግሞ በተመሳሳይ ሁኔታ እየተጓዙ በቃላት ደረጃ ይለያያሉ፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን ሁሉም ስንኞች እኩል ርዝመት ነው ያላቸው፡፡ ሁላቸውም “ሰላም ዓለይከ” በሚል ሐረግ የሚጀምሩ መሆናቸው ደግሞ የነሺዳው ኪናዊ ውበት ምንጭ ሆኗል፡፡
 
   በዚህ መጣጥፍ የምጋብዛችሁ የኦምዱርማኑን “አሕመድ ያ ሐቢቢ” ነው፡፡ ከኔ ጋር ነሺዳውን በ“ፊርቀቱ ሳሕዋ” ዜማ ለመዘመር ተዘጋጁ! ዳይ!!!
(ዐረብኛውን ወደ አማርኛ መተርጎም ይከብዳል፡፡ ስለዚህ እንዳለ ልተተው ተገድጃለሁ)፡፡
  *****  *****  *****
አሕመድ ያ ሐቢቢ ሰላም ዓለይከ
ያ ሚስኪ ወጢቢ ሰላም ዓለይከ
---
ሰላም ዓለይከ ዜይነል አንቢያኢ
ሰላም ዓሌይከ አትቀል አትቂያኢ
ሰላም ዓለይከ አስፉል አስፊያኢ
ሰላም አለይከ ሚን ረብቢ-ሰማኢ
ሰላም ዓለይከ ዳኢመን ቢላ ኢንቲሃኢ
ሰላም ዓለይከ
----
ሰላም ዐለል ሙቀደም ሊል ኢማማ
ሰላም ዐለል ሙዘለል ቢል ጘማማ
ሰላም ዐለል ሙዘወጅ ሊል ከራማ
ሰላም ዐለል ሙሰቢህ ሊል ሰላማ
ሰላም ዐለል ኹላሳ ሚን ቱሐማ
ሰላም ዐለል ሙሸፍፊዕ ቢልቂያማ
ሰላም ዓለይከ
-----
ሰላም ዐለይከ ጣሃ ያ ሐቢቢ
ሰላም ዐለይከ ያ ሚስኪ ወጢቢ
ሰላም ዐለይከ ያ -ማሂ ዙኑቢ
ሰላም ዐለይከ ያ ጃሊል ኩሩቢ
ሰላም ዓለይከ
 -----
ሰላም ዐለይከ ያ ኸይረል አናሚ
ሰላም ዐለይከ ያ በድረ ተማሚ
ሰላም ዐለይከ ያ ኑረል ዘላሚ
ሰላም ዐለይከ ያ ኩለል ጉራም
ሰላም ዐለይከ
----
ሰላም ዐለይከ ያ ዘል ሙእጂዛቲ
ሰላም ዐለይከ ያ ዘል በይናቲ
ሰላም ዐለይከ ያ ሐቢቡ ዛቲ
ሰላም ዐለይከ ያ ሐሱነ-ስ-ሲፋቲ
ሰላም ዐለይከ ያ ዙኽረል ዑሳቲ
ሰላም ዐለይከ
----
ሰላም ዐለይከ አሕመድ ያ ሙሐመድ
ሰላም ዐለይከ ያ ጣሃ ያ ሙመጀድ
ሰላም ዐለይከ ዘል መንተፈረጅ
ሰላም ዐለይከ
---
ሰላም ዐለይከ ያ ሩክነ-ሰላሂ
ሰላም ዐለይከ ያ ዘይነል ኢላሂ
ሰላም ዐለይከ ያ ዳኢል ፈላሒ
ሰላም ዐለይከ
---
አሕመድ ያ ሐቢቢ ሰላም ዓለይከ
ያ ሚስኪ ወጢቢ ሰላም ዓለይከ
  *****  *****  *****
አፈንዲ ሙተቂ
ሸገር- አዲስ አበባ
ጥቅምት 2/2006

1 comment:


  1. اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى آله وصحبه ومن اتبعه باحسان صلاة وتسليما كثيرا طيبا مباركا فيه الى يوم الدين .. آمين.

    ReplyDelete