Friday, September 25, 2015

የቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ዘመቻ ለምን?


(አፈንዲ ሙተቂ)
----




ዘመቻው የተጀመረው የዛሬ ሁለት ሳምንት ገደማ ይመስለኛል፡፡ ለመጀመሩ ምክንያት የሆነው ደግሞ “ቢቢሲ ትኩረቱን በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ላይ ያደረገ የስርጭት ፕሮግራም ይጀምራል” የሚል ዜና መነገሩ ነው፡፡ ታዲያ ይህንን ዜና ተከትሎ “የስርጭት ቋንቋዎቹ አማርኛ እና ትግርኛ ናቸው” የሚል ወሬ ተደመጠ፡፡ ነገሩ እስከ አሁን ገፍቶ ባይመጣም በትክክል ተብሎ ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም የውጪ ሰዎች እንዲህ ዓይነቱን ነገር ለመወሰን ሲነሱ በቅድሚያ የሚያዩት በየሀገራቱ ውስጥ በኦፊሴል የሚሰራባቸውን ቋንቋዎች ነው፡፡ ትግርኛ በኤርትራ፣ አማርኛም በኢትዮጵያ የኦፊሴል ቋንቋ የመባል ደረጃ ያላቸው በመሆናቸው ቢቢሲ በዚሁ ምክንያት ፕሮግራሙን በሁለቱ ቋንቋዎች ለማስተላለፍ ወስኖ ሊሆን ይችላል፡፡ በየሀገራቱ ውስጥ ያሉት ቋንቋዎች ተናጋሪ ብዛት ሲታይ ግን አፋን ኦሮሞ ከሁሉም ይቀድማል፡፡

እንደሚታወቀው በሬድዮ የሚተላለፍ ፕሮግራም የሚሻው አድማጭ እንጂ አንባቢ አይደለም ፡፡ ስለዚህ በኤርትራና በኢትዮጵያ ላይ የሚያተኩረው አዲሱ የቢቢሲ የስርጭት ፕሮግራም አድማጮችን ታሳቢ ያደረገ መሆን ይገባል፡፡ እናም ይህንን ያዩ ተመልካቾች “ቢቢሲ የቪኦኤን ሞዴል መከተል ይገባል፤ አፋን ኦሮሞም ከሁለቱ ቋንቋዎች ጋር መደመር አለበት” በማለት በኢንተርኔት የድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብ ጀመሩ፡፡ እኛም ዘመቻው ተገቢ ሆኖ ስላገኘነው ፊርማችንን ሰጠነው፡፡ ሌሎችም እንዲፈርሙ መቀስቀሱንም ተያያዝነው፡፡

በእስካሁኑ ሂደት የፈረመው ሰው ብዛት ወደ ሳላሣ ሺህ እየተጠጋ ነው፡፡ በኢንተርኔት ላይ ሆነን እንደታዘብነው ሂደቱ በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው፡፡ ሁሉም ወገኖች ዘመቻውን በበጎ መልኩ እያዩት ነው፡፡ እነ አትሌት ደራርቱ ቱሉ እና ዓሊ ቢራን የመሳሰሉ ታላላቅ ሰዎችም የድጋፍ ፊርማቸውን ሰጥተዋል፡፡ ሌሎችም ድጋፍ እንዲሰጡም እየቀሰቀሱ ነው፡፡ ይህ በጣም ጥሩ ነው፡፡ በተለይም የኢንተርኔቱ ዓለም ከሚታወቅበት “ጽንፋዊ” (polarized) አካሄድ ወጥተን ሁላችንም ፊርማችንን ማኖራችን በእጅጉ የሚያስደስት ነገር ነው፡፡
---
የድጋፍ ፊርማችንን ያኖርነው በሙሉ በጎን የማሰብ ዓላማ እንጂ ሌላ ተቀጥላ መነሻ የለንም፡፡ ታዲያ እነዚህ ምክንያቶች በደንብ የተብራሩ ስላልመሰለኝ ይህንን ጽሑፍ አሰናድቼአለሁ፡፡

እንደሚታወቀው “አፋን ኦሮሞ” (ኦሮምኛ) በአፍሪቃ ምድር እጅግ ብዙ ተናጋሪዎች ካሉት ቋንቋዎች አንዱ ነው፡፡ 40 ሚሊዮን የሚሆን ህዝብ ቋንቋውን በአፍ መፍቻነት ይናገረዋል፡፡ ከስድስት ሚሊዮን የማያንሱ ህዝቦችም ኦሮምኛን በሁለተኛ ደረጃ ይናገራሉ፡፡ ይሁንና ኦሮምኛን ከሚናገረው ህዝብ መካከል ከ3/4 የሚልቀውና በገጠር የሚኖረው ህዝብ ከኦሮምኛ ውጪ ሌላ ቋንቋን አይናገርም፤ አይሰማም (ነገሩን በተነጻጻሪነት ለማወቅ ካሻችሁ የኦሮሚያ ክልል የህዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤትን ይመልከቱ)፡፡ ስለዚህ የቢቢሲ ስርጭት ኦሮምኛን ከዘነጋ ይህ ህዝብ ቢቢሲ የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ላይሆን ነው ማለት ነው፡፡

ታዲያ የሚገርመው ደግሞ በሬድዮ የሚሰማውን ፕሮግራም ከማንም በላይ የሚከታተለው የገጠሩ ህዝብ ነው፡፡ የከተማው ህዝብ በዝንባሌው ለቴሊቪዥን፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህም ለኤፍ ኤም ሬድዮ ነው የሚያደላው፡፡  ቢቢሲ በሬድዮ ፕሮግራሙን ሲጀምር ተጨማሪ አማራጭ የሚፈጠርለት በአብዛኛው ለገጠሬው ህዝብ ነው፡፡ ነገር ግን ኦሮምኛ ከአዲሱ ፕሮግራም ውስጥ ከተዘነጋ የገጠሩ የኦሮሞ ህዝብ ሌሎች ቋንቋዎችን ባለመቻሉ እድሉ ሊያመልጠው ነው፡፡ እንግዲህ ቢቢሲ አፋን ኦሮሞን በስርጭት ሽፋኑ ውስጥ እንዲያካትት በድጋፍ ፊርማ መጠየቁ የተፈለገበት አንደኛው ምክንያት ይህ ነው፡፡

ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ለህዝቡ አማራጭ የመፍጠር ጉዳይ ነው፡፡ ይህም ከላይ የተገለጹትን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የኦሮምኛ ተናጋሪዎች የሚመለከት ነው፡፡ እንደሚታወቀው በሶስተኛው ዓለም ሀገር በአጭር ሞገድ የሚተላለፉ ሬድዮዎች በመንግሥታት የተያዙ በመሆናቸው ህዝቦች መረጃን ከነጻ ምንጭ የማግኘቱ ጉዳይ ይቸግራቸዋል፡፡ በግል፤ በፖለቲካ ፓርቲ እና በኮሚኒቲ እየተቋቋሙ ወደ አፍሪቃ ምድር ስርጭታቸውን የሚያስተላልፉ ሚዲያዎችም መንግሥታቱን ለማጋለጥ በሚል ነገሮችን ከልክ በላይ እየለጠጡና እያጋነኑ ለአድማጩ ስለሚተርኩ ግራ መጋባትንና መደናገርን ይፈጥራሉ፡፡ ቢቢሲ፣ ቪኦኤ፣ ዶቼ ቬሌ ወዘተ.. የመሳሰሉት ግን ከሁሉም የተሻሉ ነጻ ሚዲያዎች በመሆናቸው በነርሱ የሚተላለፉት ዘገባዎች ለእውነታ የቀረቡ መሆናቸው ይታመናል፡፡ እናም ቢቢሲ በአፋን ኦሮሞ ፕሮግራም ጀመረ ማለት ኦሮምኛን የሚሰማውና የሚናገረው ህዝብ ነጻ መረጃ የሚያገኝበት እድል ጨመረ ማለት ነው፡፡

ሶስተኛው ምክንያት ደግሞ የቢቢሲ በኦሮምኛ ፕሮግራም መጀመር ለአፋን ኦሮሞ እድገት ወሳኝ ሚና የሚጫወት መሆኑ ነው፡፡ ቢቢሲ ሁሉንም አቀፍ እና በቢሊዮን የሚቆጠሩ አድማጮች ያሉት ተቋም ነው፡፡ ፕሮግራሙ በተመራጭነቱ ቀዳሚ እንዲሆን ያስቻለው በሚያስተላልፈው ጭብጥና ይዘት ብቻ ሳይሆን ቀዳሚነቱን ለማስቀጠል በሚያከናውናቸው ተያያዥ መርሐ ግብሮች ጭምር ነው፡፡ ከነዚህም አንዱ ስርጭቱን የሚያስተላልፍባቸው ቋንቋዎችን ለማዘመን፣ ለማሳደግ እና ለማስተዋወቅ የሚያደርጋቸው ጥረቶች ናቸው፡፡ ተቋሙ ፕሮግራሙን ሲያስተላልፍ የዘፈቀደ የቋንቋ አጠቃቀምን አይከተልም፡፡ ቢቢሲ እያንዳንዱን ቋንቋ በማጥናት የቋንቋው አድማጮች ሁሉ ሊረዱት የሚችሉትን አቀራረብ ይወጥንና በዚያ መሰረት ስርጭቱን ያስተላልፋል፡፡ ራሱ የሚገለገልበት BBC-Standard የተባለ የቋንቋ አጠቃቀም ዘይቤም አለው፡፡

 በሌላ በኩል ቢቢሲ ስርጭቱን በሚያስተላልፍባቸው ቋንቋዎች ዙሪያ በሚደረጉት ምርምሮችም ተሳትፎ ያደርጋል፡፡ ቋንቋውንም ለማስተማር ልዩ ልዩ ጥረቶችን ያደርጋል (ለምሳሌ የቢቢሲ የዐረብኛው ፕሮግራም Learn BBC Arabic የተባለ ፕሮግራም አለው)፡፡ በቋንቋው የሚሰለጥኑ ተማሪዎችንም ይደግፋል፡፡ በቋንቋው የሚጻፉ የስነ-ጽሑፍ ውጤቶችን ያበረታታል፡፡ በሬድዮ ጣቢያውም ድርሰቶቹን ያስተዋውቃል፡፡ እነዚህ ተግባራት ለኦሮምኛ ቋንቋ እድገት እጅግ በጣም ይጠቅማሉ፡፡

እንግዲህ “ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ” የተሰኘውን ዘመቻ ለመደገፍና ሌሎችም ድጋፋቸውን እንዲሰጡት ለመቀስቀስ የወሰንኩት እነዚህን ሁሉ መነሻዎች ካጤንኩ በኋላ ነው፡፡ በመሆኑም ለቋንቋው እድገት የሚቆረቆር እና በተለይም በገጠሩ የሚኖረው ህዝባችን አማራጭ ሚዲያ እንዲፈጠርለት የሚሻ ሰው በሙሉ ሊሳተፍበት የሚገባ ታሪካዊ ዘመቻ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ከዚህ ቀደም “ኦሮምኛን መማር እፈልጋለሁ” ፣ “ኦሮምኛ ከሌሎች ቋንቋዎች ጋር ያለው ተዛምዶ ለማጥናት ወስኛለሁ”፣ “የዓሊ ቢራን ዘፈን ግጥሞች ትርጉም ማወቅና በርሱ ዙሪያ መጻፍ እሻለሁ” ወዘተ… ስትሉኝ ለነበራችሁት ወዳጆቼ ደግሞ ዘመቻው የናንተንም ሆነ ተመሳሳይ ፍላጎትና ዝንባሌ ያላቸው ሌሎች ሰዎች ምኞቸውን  እውነት ሊያደርጉ የሚችሉበትን ውጤት ለማምጣት የሚረዳ በመሆኑ ተሳትፎአችሁ በእጅጉ ይጠበቃል፡፡
---
ይህ ዘመቻ ማንንም የመጉዳት ዓላማ የለውም፡፡ ዘመቻውን የጀመሩት ሰዎችም ሆኑ በሂደት የተቀላቀሉት ሁሉ ይህንን ጉዳይ በይፋ አስታውቀዋል፡፡ እያሳወቁም ነው፡፡ እኔም ደግሞ አስታውቃለሁ፡፡ ለምሳሌ ቢቢሲ የአማርኛውንም ሆነ የትግርኛውን ፕሮግራም እንዲያስቀር በጭራሽ አልተጠየቀም፡፡ ሊጠየቅም አይችልም፡፡ እንዲህ ብሎ መጠየቁ ከመጥፎ ምሳሌነቱ ሌላ ጥያቄው ተቀባይነት እንዳይኖረው ማድረግ ነው፡፡ ጥያቄው የቀረበው ቢቢሲ የቪኦኤን አርአያ በመከተል ስርጭቱን በሶስቱ ቋንቋዎች እንዲጀምር ነው (ስርጭቱን የሚያስተላልፍበትን የጊዜ መጠን የመወሰኑ ስልጣን የጣቢያው ነው፤ ያንን እኛ አንወስንለትም)፡፡ በመሆኑም ይህ በግልጽ ሊታወቅ ይገባል፡፡
----
ስለዚህ ወዳጆቻችን ሆይ!

ይህ የዘመቻ የተቀደሰ ሃሳብ ያለው ነው፡፡ የድጋፍ ፊርማችሁን በማኖር የዘመቻው ደጋፊ እንድትሆኑ በአክብሮት ትጠየቃላችሁ፡፡ ለዚህ ደግሞ መሰዋት አያስፈልጋችሁም፡፡ ሶስት ደቂቃ ብቻ ወስዳችሁ ለዚህ የተዘጋጀውን petition መፈረምንና ወደሚፈለግበት ቦታ send ማድረግን ብቻ ነው የሚጠይቀው፡፡ እናም ቀጥሎ የተመለከተውን ሊንክ ከፍታችሁ ፔቲሽኑን ፈርሙልን!! ዳይ

https://www.gopetition.com/petitions/bbc-consider-afan-oromo-for-new-broadcasts-to-ethiopiaeritrea-as-a-matter-of-priority.html#fbbox
----
ማስታወሻ
ፔቲሽኑን መፈረም ማለት ሊንኩን ከፍቶ ፎርሙን መሙላት ነው::  ስለዚህ ሊንኩን ከፍታችሁ ፔቲሽኑን ፈርሙልን፡፡

ፔቲሽኑን ለመፈረም የግዴታ የኤ-ሜይል አድራሻችሁን ማስገባት አለባችሁ፡፡ ከዚያም የቀረቡትን ጥያቄዎች በመከተል ፎርሙን መሙላት ይገባችኋል፡፡ መጨረሻ ላይ የተሞላውን ፎርም send አድርጋችሁ ስታበቁ ፊርማውን ስለመስጠታችሁ ማረጋገጫው በኢ-ሜይል ይላክላችኋል፡፡

ይህንን አጭር ጽሑፍ “ሼር” በማድረግ ብትተባበሩን ደግሞ የበለጠ እንፋቀራለን፡፡

Wednesday, September 23, 2015

“ዐረፋ” እና “ዒድ አል-አድሐ”

ፀሐፊ ፡ አፈንዲ ሙተቂ
---
በ1982 ነው፡፡ ባልሳሳት ዕለቱ ሰኔ 26 ይመስለኛል፡፡ የኢድ አል አድሐን በዓል ለማክበር በገለምሶው የሼኽ ዑመር ዓሊይ ሐድራ ተሰብስበናል፡፡ የዕለቱ የክብር እንግዳ የሐብሮ አውራጃ ኢሠፓ ኮሚቴ አንደኛ ጸሐፊ የነበሩት ጓድ ዓለሙ መንገሻ ነበሩ፡፡ የመድረክ መሪው ጓድ ዓለሙን ንግግር እንዲያደርጉ ጋበዛቸው፡፡ እሳቸውም ንግግራቸውን እንዲህ በማለት ጀመሩ፡፡

“የአረፋ በዓል ታላቅ በዓል ነው፡፡ የእስልምና እምነት እንደሚያስተምረው ዐረፋ የሚለው ቃል በዐረብኛ “አወቀ” እንደማለት ነው፡፡ ይህም ታሪክ አለው፡፡ አዳምና ሔዋን ወይንም አደምና ሀዋ ከጀንነት ወደ ምድር ከወረዱ በኋላ ለብዙ ዘመናት ተጠፋፍተው ነበር፡፡ ለረጅም ጊዜ ሲፈላለጉ ከቆዩ በኋላ በዚህ ዕለት በሳዑዲ ዐረቢያ ባለው የአረፋ ተራራ ላይ ተገናኙ፡፡ እዚያም “ዐረፍቱከ… ዐረፍቱኪ” ተባባሉ፡፡ “አወቅኩህ! አወቅኩሽ” ማለታቸው ነው፡፡ ይህንን ታሪክ ለመዘከር ሲባል ነው የዐረፋን በዓል ማክበር የተጀመረው”

ጓድ ዓለሙ የገለጹት ታሪክ የሚመለከተው የዙልሒጃን ወር ዘጠነኛ ቀን ነው እንጂ አስረኛውን ቀን አይደለም፡፡ ነገር ግን ይህንን ታሪክ ከሙስሊም ዓሊሞች ሳልሰማው ከእሳቸው አንደበት መስማቴ በጣም ደንቆኛል፡፡ ለዚያውም የሳቸው ፓርቲ በይፋ “ኤቲይዝምን” የሚሰብክ ሆኖ እያለ ነው እሳቸው ታሪኩን ያወጉን፡፡

እውነት ነው፡፡ ሐጅ በሚባለው አምስተኛው የእስልምና ማዕዘን (አርካን) ውስጥ ከሚፈጸሙት መንፈሳዊ ስርዓቶች መካከል በዙልሒጃ ወር ዘጠነኛ ቀን የሚከናወነው “አል-ዉቁፍ ቢዐረፋት” (በዐረፋ ቆሞ ጸሎት ማድረግ) ቀዳሚው መሰረቱ ከነቢዩ አደም ጋር የተገናኘው ታሪኩ ነው፡፡ ከመላው ዓለም የተሰባሰቡ ሐጃጆች ብሄር፣ ጾታ፣ ቀለም፣ አህጉር፣ ሀገር፣ ክፍለ ሀገር፣ መደብ፣ ስልጣን፣ የስራ መደብ፣ ወዘቱ ሳይገድባቸው በአንድ ቦታ ቆመው ሁላቸውም የአዳም ልጆች መሆናቸውን ያስመሰክራሉ፡፡

ታዲያ በዚሁ ቀን ሁለት ትልቅ ድርጊቶች ተከናውነዋል፡፡ ከነዚህም መካከል አንዱ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በታሪክ ገጾች The Masterpiece Sermon of Mohammed እየተባለ የሚጠራውን ታላቅ ዲስኩራቸውን ያሰሙበት እለት መሆኑ ነው፡፡ ነቢዩ ንግግራቸውን የጀመሩት “ሰዎች ሆይ! ከዚህ በኋላ በናንተ መካከል ላልገኝ እችላለሁ፤ ስለዚህ ልብ ብላችሁ አድምጡኝ” በሚል ዐረፍተ ነገር ነው፡፡ በርግጥም ነቢዩ ከዚህ የመሰናበቻ ንግግራቸው በኋላ በህይወት ብዙም አልቆዩም፡፡ ቢሆንም ከነቢዩ ንግግሮች መካከል በደንብ የተመዘገበው ይህ ንግግራቸው ነው፡፡ በሐዲስ ምሁራን ዘንድ የቃላትና የሐረጋት ልዩነት ሳይደረግበትና በእውነተኛነቱ ላይ ጥርጣሬ ሳይጣልበት (“ሰሒሕ” እና “ደዒፍ” ሳይባል) ተቀባይነትን ያገኘው ይህ የሐጀቱል ወዳዕ ንግግራቸው ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ንግግሩ በመቶ ሺህ ህዝብ የተሰማ መሆኑ ነው፡፡
   
ይህ ቀን የሚታወስበት ሁለተኛው ታላቅ ክስተት የቅዱስ ቁርአን የመጨረሻው አያህ (አንቀጽ) የወረደበት ዕለት መሆኑ ነው፡፡ አዎን!! “ኢቅራእ” በሚለው መለኮታዊ ቃል የጀመረው መጽሐፍ በዚህ ዕለት በሱረቱል ማኢዳ ውስጥ በሚገኘው ሶስተኛው አንቀጽ ተጠናቅቋል፡፡ በዚሁ አንቀጽ ውስጥ እስላማዊውን ርእዮት ለዓለም የማዳረሱ ተልዕኮ በከፍተኛ ስኬት መጠናቀቁን የሚገልጸው ዐረፍተ ነገር ይገኛል፡፡ እንዲህም ይላል፡፡
“ዛሬ ለናንተ ሃይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ፤ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፤ እስልምናንም በሃይማኖትነት ወደድኩላችሁ”
(ሱረቱል ማኢዳ፤ 3)
---
ነቢዩ ሙሐመድ እንዲህ ብለዋል
“በዐረፋ ቀን ለጾመ ሰው አላህ ያለፈውን ዓመትና የቀጣዩን ዓመት ሐጢአቱን ይቅር ይለዋል”

በኛ ሀገር በተለምዶ ዐረፋ የሚባለው የኢድ አል አድሓን በዓል የምናከብርበት አስረኛው እለት ነው፡፡ በሸሪዓው እይታ ግን ዐረፋ የሚባለው የዙልሒጃ ወር ዘጠነኛው ቀን ነው፡፡
--
የዒድ አል-አድሓ ታሪካዊ ዳራ ደግሞ ነቢዩ ኢብራሂም ልጃቸውን ለአላህ ለመሰዋት ያደረጉት ቁርጠኝነት የተመላበት ውሳኔ እና ለመስዋዕትነት የቀረበው ልጅ ያሳየው የተለየ ጽናት ነው፡፡ ነቢዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) የበኩር ልጃቸው የሆነውን ዒስማኢልን (ዐ.ሰ.) ያገኙት በእርጅና ዘመናቸው ነው፡፡ ታላቅ ሚስታቸው ሳራ ለፍሬ ባለመብቃቷ “ያ አላህ ያለ ዘር አታስቀረኝ፤ እኔን የሚተካ ሷሊህ የሆነ ልጅ ስጠኝ” በማለት ዱዓ አደረጉ፡፡ በዚሁ መሰረት በሳራ ፈቃደኝነት ሐጀራ የምትባለውን የቤት ሰራተኛቸውን አገቡ፡፡ ሐጀራም ዒስማኢል የተባለ ልጃቸውን ወለደችላቸው፡፡ ይህ ልጅ በአላህ ፈቃድ በመካ ከተማ እንዲያድግ የተወሰነ ስለነበረ ኢብራሂም ሐጀራን እና ዒስማኢልን ወደ ዐረቢያ ከተማ ወሰዷቸው፡፡

ዒስማኢል ካደገ በኋላ ደግሞ አላህ “ልጅህን እንድትሰዋ ታዘሃል” የሚል ትዕይንት በህልማቸው አሳያቸው፡፡ የነቢያት ህልም ደግሞ ከራዕይ የሚቆጠር ነው፡፡ ስለዚህ ኢብራሂም በህልማቸው ያዩትን በዝምታ አላለፉትም፡፡ በወቅቱ የሆነውን ቅዱስ ቁርኣን እንዲህ ይተርካል፡፡

“ከርሱ ጋር ለስራ በደረሰ ጊዜም “ልጄ ሆይ! እኔ በህልሜ የማርድህ ሆኜ አይቻለሁ፤ (እስቲ አንተም ነገሩን) ተመልከት፡፡ “ምን ይታይሃል” አለው፡፡ (ልጁም) አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ፈጽም፤ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ አለ”
(ሱረቱ -ሷፍፋት፤ 102)

አባትና ልጅ በዚህ መንገድ ከአላህ የተላለፈውን ትዕዛዝ ሊፈጽሙ ተነሱ፤ ነቢዩ ኢብራሂም ልጃቸውን እንዲሰው የታዘዙት ከዐረፋት መሬት ብዙም ባልራቀ ቦታ ላይ ስለነበረ ወደዚያው ጉዞ ጀመሩ፡፡ በመንገዳቸው ግን ኢብሊስ በሰው ተመስሎ በጣም ተፈታተናቸው፤ ሶስት ጊዜ ያህል እየወጣ “ከስንት ዓመት በኋላ ያገኘኸውን አንድዬ ልጅህን ስትሰዋ ምንም አይጸጽትም?… እንዴት ጅል ትሆናለህ” እያለ ሞገታቸው፡፡ ከአላህ ትዕዛዝ ፍንክች የማይሉት ኢብራሂም ግን ድንጋይ ከመሬት በማንሳት “አዑዙቢላሂ ሚነ-ሸይጣኒ ረጂም” እያሉ ኢብሊስን ወገሩት፡፡

ኢብራሂም ዒስማኢልን ሊያርዱት አጋደሙት፡፡ ልጁም ምንም ሳያንገራግር ከመሬቱ ላይ ተኛ፡፡ ኢብራሂም ልጁን ሊያርዱት ሲሞክሩ ግን ቢላዋው አላርድ አላቸው፡፡ ኢብራሂም እንደገና ቢላዋውን ገዘገዙት፡፡ ነገር ግን ቢላዋው ፈጽሞ ዶለዶመ፡፡ ልጁ የሆነው ነገር አልገባውም፡፡ አባቱ ቶሎ ስላላረደው ተገረመና “አባዬ! ፣ ምናልባት የአባትነት ፍቅር ይዞህ ይሆናል በቶሎ ያላረድከኝ፤ እስቲ ዐይኔን በጨርቅ ሸፍነውና እርዱን ሞክር” የሚል አስተያየት ሰጠ፡፡

በዚህን ጊዜ ግን ከወደ ሰማይ ጥሪ መጣ፡፡ የአላህ መልአክ “ኢብራሂም ታላቅነትህን አስመስክረሃልና እርዱን አቆየው” በማለት አወጀ፡፡ በምትኩም መልአኩ ከገነት ያመጣውን በግ እንዲያርድና ልጁን ወደቤቱ እንዲወስደው ነገረው፡፡ በዚህም መሰረት በጉ ታረደ፡፡ ኢብራሂምና ዒስማኢልም ወደ መካ ከተማ ተመለሱ፡፡ ሁለቱ ሰዎች ለፈጣሪ መታዘዝን በግልጽ ያሳዩባት ያቺ ዕለት የዒድ አል-አድሓ በዓል ሆና እንድትከበርም ተወሰነ፡፡ ዒስማኢል ለመስዋእትነት የቀረበበት ድርጊት ደግሞ በዚሁ ዕለት የሚታረደው “ኡድሒያ” መነሻ ሆነ፡፡
----
ዒድ አል-አድሐ የመስዋዕትነትና የመዳን በዓል ነው፡፡ የሐጅ ጸሎት የሚፈጽም ሰው በዚህ ዕለት “ኡድሒያ” የማረድ ግዴታ አለበት፡፡ እኛም ወደ ሐጅ ያልሄድነው ደግሞ ከተቻለ በዚሁ ዕለት በየቤታችን እንስሳት እያረድን ለ“ኡድሒያ” እንድናቀርብ ታዘናል፡፡ ታዲያ ኡድሒያው “ኡድሒያ” ተብሎ የሚመዘገብልን እርዱም ሆነ አጠቃቀሙ ነቢዩ ያስተማሩትን መንገድ የተከተለ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ለምሳሌ አንዳንድ ሰዎች ፍየሉን ያርዱና ለበዓል የሚሆናቸውን ያህል ካስቀሩለት በኋላ ሌላውን ወደ ፍሪጅ ውስጥ ይከቱታል፡፡ ይህ ግን ራስን መጋበዝ ነው እንጂ ኡድሒያ ተብሎ አይመዘገብም፡፡

ነቢዩ እንዳስተማሩት ለኡድሒያ ከታረደው ስጋ አንድ ሶስተኛው በቀጥታ ለድሆች መከፋፈል አለበት፡፡ አንድ ሶስተኛው ለዘመድና ለወዳጅ ነው የሚሰጠው፡፡ የተቀረው አንድ ሶስተኛ ብቻ ነው ለቤተሰቡ አገልግሎት የሚውለው፡፡ ስለዚህ በዚህ እለት የሚፈጸመው መስዋእት “ኡድሒያ” ሆኖ እንዲመዘገብልን ካሻን ትክክለኛውን መንገድ መከተል አለብን፡፡ በተለይ ከታረደው ስጋ የድሆች ድርሻ የሆነውን “ሡሉሥ” ከሁሉም አስቀድመን ለባለቤቶቹ እናስረክብ ዘንድ የአደራ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

ዒድ ሙባረክ
አፈንዲ ሙተቂ
----
መስከረም 12/2008
ሀረር-ምስራቅ ኢትዮጵያ
----


Sunday, September 20, 2015

Mirriga- An Elite Song of the Oromo People

Mirriga- An Elite Song of the Oromo People
----
Written by : Afendi Muteki
----
Mirriga (also called “Mirriysa) is an epic song very popular among the Eastern Oromos. It is commonly known in the traditions of the tribes of Ittu, Karrayyu and Afran Qalloo. However, from these three groups, Mirriga highly deepens its root among the Ittu Oromos of Carcar (West Harerghe). The reason is that “Ittu” is the Oromo group to whom the foundation and preservation the famous Oda Bultum is ascribed, and Mirriga is the main genre of a song that dominates the events commemorating the ancient caffee assembly of Oda Bultum.

“Mirriga” is considered the power house of knowledge and wisdom. The Ittu Oromos say that their tradition, customs, history and ethics are highly enshrined in the Mirriga song. Furthermore, many of the Ittu Oromo tribal laws can be learned easily from the Mirriga poems. Thus the Ittus Oromos say

Fooni nyaatti malee adurree ilkaan meetaa
Namaatu hinbeyne malee mirrigaa kheessi heera.

Meaning
The cat eats a meat yet her teeth are “silver”
Mirriga is a law internally, yet many people don’t understand.

Mirriga is a highly elicitic song that can’t be sung by everybody except those who have a knowledge. It isn’t sung also at everywhere. It is usually performed on two occasions. One is when a senior leaders of a clan and the men at their service come together to discuss an issue that needs consideration at a clan level, or when the leaders and deputies of all clans of Ittu Oromo discuss a tribal issue. The other occasion is the one I said above. That is the celebration of special events like the congress of Oda Bultum.
*****
The Mirriga poems are of two types, the existing (traditional) poems and the non-traditional ones. The traditional poems are those which have been transmitted orally from one generation to the next. The themes of these poems are the Oromo history, culture, tradition and law. These traditional poems are known by most of the clan leaders of Ittu Oromo although there may be variations on the usages of the words of the poems. For a person to be elected as a leader of a clan, the other posts in the leadership of the clan, to be the member of the congress of Oda Bultum or to be elected in the tribal office of Ittu Oromo, he must have a good knowledge of the traditional Mirriga poems. The best example of the traditional Mirriga poem is the following one which the Ittu Oromos regard as “The golden Constitution of Oda Bultum”

Afuriin Odaa bule shaniin “Darrabbaa” bule
Darraabbaa halkan heeraa gaariin maal hasaasaa bule
Okholee saddeetin heeree, okkotee saddeetin heeree
Khorma saddeet heeree, khilla saddeet heeree
Ciicoo saddeet heeree, haqaaraa saddeet heeree
Siinqee saddeet heeree, Dhibaayyuu saddeet heere
Waraana saddeetiin heere, fal’aana saddeetin heeree
Eela saddeet heere, goojjoo saddeet heeree
Daadhii Bookhaa nannaqee, deyma wal-kheessa tufe
Mee akka galaana kufee siitu garaa nadhufe.
-----
The poem can be translated as follows.

The four have passed the night at Odaa, the five passed the night at Darrabaa
What did the “wise” whispered in the law-making night of Darrabbaa?
He Decreed eight “Okholee”, and eight pots
He decreed eight bulls and eight “Khilla”
He decreed eight “Ciicoo” and eight “Haqaaraa”
He decreed eight Siinqee and eight “Dhibaayyuu”
He decreed eight spears and he decreed eight spoons
He decreed eight wells and eight huts
He prepared a drunk from pure honey, and he breath the same
Oh my blood! You have come to my mind as a traveling flood.

In the poem, the verse “the four have passed the night at Odaa” refers to the four clans composing the “Galaan” moiety of Ittu Oromo.  They are called Baabbo, Alga, Gaadulla and Elelle. According to the tradition of Oda Bultum, these four clans discuss and draft new laws under the oda tree (Qallu is the fifth clan grouped under this moiety but it is prohibited by the tradition to participate in political affairs; thus the Qallu clan don't participate in the formulation of new laws and the assumption of political power. Qallu are usually the religious leaders of the people).

“The five who passed the night at Darrabba” refers to the five clans consisting the “Khura” branch of Ittu Oromo. They are called Addayyo, Waayye, Gaamo, Arroojjii and Baaye. These five clans discuss new laws under “Garbii Darrabbaa”- a big acacia tree found two kilo meters north of Oda Bultum. The law drafted at the two places will be brought together at Oda Bultum for the ratification by the tribal assembly. It was only after this process was accomplished that the new laws would be proclaimed at Oda Bultum in the last night of the event.

The other verses of the poem refer to the items (Khilla, Khorma, Haqaara) and materials (okholee, okkotee, waraana, siinqee, goojjoo etc) needed to undertake certain ritual ceremonies at Oda Bultum. These rituals were undertaken side by side with the drafting of new laws.  The poem says “the eight” because only eight clans undertake these rituals and two clans of Ittu Oromo were exempted from conducting the rituals. One of the two clans exempted from the rituals was the Waayyee clan who had a responsibility of monitoring the security during the celebration of the congress of Oda Bultum. The second clan was the Qallu who are regarded the people of blessing and healing.
*****
The non-traditional Mirriga poems are those which are composed on specific events or those which an individual poet-singer called “qondaala” composes on his own will. Most of these poems are short lived; they have little chance of spreading in the society and establishing themselves at equal level with the traditional poems. However, they are the determinants in examining the wisdom and eloquence of the “qondaala”. They are also some of the denominators that determine the status the “qondaala” will have in the society and the future prospects he may assume. If the “qondaala” is an incumbent leader of an Ittu clan, then the fame he would get because of his poems may bring him more respects; moreover, his role as a clan leader may increase.  If the “qondaala” that composes the new exciting poems is of young age, then it is very likely for him to be the future leader of his clan and to get a place in the leadership of Oda Bultum.

Although it heavily relies on the poetry skills of “qondaala”, Mirriga is not a solo song; it is performed by a group. Its performance requires usually the elites (hayyuu) of a clan or certain group gathered in a house or under a shade of a tree. When the singing starts, the qondaala (poet-singer) of the clan stands within the crowd by holding his “halangee” (a whip made from skin) and howls the rhythmic Mirriga poems. He starts his singing by the famous two verses.

Dhagayi Dhageeffadhu (Hear me, and Listen to me)
Guurii gurraa guuradhu (Take way the dust from your ears)

Then after, he starts his singing. Whenever he utters one verse of the poem, the crowd will accompany him by replaying with the famous Oromo word “hayyee” (meaning “let it be”). And when the “qondaala” show his ability by composing an extra ordinary poem, the members of the crowd will express their excitement by words like “buli” (long live), “kormoomi” (be strong as a roaring bull), “irra aani” (be able to defeat your enemy) etc…..

The best place where one can see the Mirriga in its natural beauty is a clan assembly. This clan assembly is usually lead by the leader of the clan called “abba gosaa” or more commonly “damiina”. The “damiina” is assisted by councilors called “hayyuu”. The “qondaala”, who are known for their Mirriga skills, also act as assistants of the “damiina”. It is the presence of such skilled people in the assembly that would be the source of the beauty of Mirriga.

It must be noted that the clan assembly wouldn’t be gathered for a mere purpose of singing Mirriga. There should be other reasons for hayyus (clan leaders, elders and other elites) to meet at certain place and deal at a clan level. For example, the hayyus may assemble to find solutions for a dispute between two people or to collect finance to be paid as a blood money of a killed person. This act is usually called “gosa bulchuu” (letting the clan to pass the night at certain place or house). The event is sponsored by the person who summoned the clan leaders to resolve his issue; and the clan assembly holds its meeting until it finds out the best way of resolving the problem. It is after the accomplishment of this task that the clan assembly opens the way for Mirriga. And wherever an act of “gosa bulchuu” took place, it is common to see a performance of Mirriga. Thus the Ittu Oromos say

Bakka guuzni oole darasiidhaan beekhani
Bakka gosti bulte ammo mirrigaadhaan beekhani

It can be translated approximately as follows

A place where guuzaa passed the day is known by the voice of “Darasii”
A place where the clan passed the night is known by the performance of Mirriga
---
The Mirriga poems are some of the best preserved examples of the ancient Oromo customs. They are still being transmitted by oral narrations. However, as they are the stores of Oromo tradition and history, they should be documented and made ready for further ethnographic studies.

Afendi Muteki
September 20/2015
Harar