Sunday, May 12, 2013

“አሚር ኑር ሙጃሂድ” እና “ጁገል” (ጀጎል)



 ጸሓፊ፡- አፈንዲ ሙተቂ

  የሀረር ከተማን ጥንታዊ ክፍል ለአምስት ምዕተ ዓመታት ከቦ የሚታየውን የጁገል (ጀጎል) ግንብ ያሰራው አሚር ኑር ሙጃሂድ ነው። የአሚር ኑር አባት ከኢማም አሕመድ ኢብራሂም አል-ጛዚ (ግራኝ) ሚኒስትሮች መካከል አንዱ የነበረው ወዚር ሙጃሂድ ዓሊ ሲሆን ይህ ሰው ኢማሙ ሐበሻን ለማቅናት ባደረገው ታላቅ ዘመቻ ውስጥ ቁልፍ ሚና ነበረው። በአንድ ወቅትም የቤጌምድር (ጎንደር) አስተዳዳሪ ሆኗል።
   የአሚር ኑር እናት የኢማም አሕመድ (ግራኝ) እህት ናት። ኢማሙ ከመሞቱ በፊት አሚር ኑርን በጣም ይወደውና  ከሌሎች ልጆችም የበለጠ ያቀርበው እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ። በዚህም የተነሳ አሚር ኑር ዘወትር ከኢማሙ አጠገብ አይጠፋም ነበር።
    ኢማም አሕመድ በ1543 ዓ.ል. በዘንተራ (ወይና ደጋ) ጦርነት ሲገደል አሚር ኑር ከዲል ወንበራ (የኢማሙ ሚስት) ጋር  በመሆን አስከሬኑን ካስቀበረ በኋላ ወደ ሀረር ተመለሰ። ከጥቂት ቆይታ በኋላ ዲል ወንበራን ለጋብቻ ሲጠይቃት የአጎትህን ደም ከተበቀልክልኝ ብቻ ነው የምታገባኝ አለችው። አሚር ኑርም ቅድመ ሁኔታውን ተቀብሎ ከአጼ ገላውዴዎስ ጋር ለመጋጠም ወደ ፈጠጋር (መካከለኛው ኢትዮጵያ) ዘመተ። ከአጼው ጋር ባደረገው ውጊያም በለስ ቀንቶት ድል አደረገ። አጼ ገላውዴዎስም በውጊያው ላይ ሞተ።
  አሚር ኑር በድል አድራጊነት ወደ ሀረር ሲገባ ከተማው በከፊል ተቃጥሎና ሱልጣን በረካት ዑመርዲን የሚባለውን የወላስማ ገዥ ጨምሮ በርካታ ሰዎች ተገድለው ጠበቁት። ይህንን ውድመት በከተማዋ ላይ ያደረሰው ራስ ሐመልማል የሚባለው የአጼ ገላውዴዎስ የጦር አበጋዝ (የአጼው የአጎት ልጅ) ነበር። አሚር ኑር የከተማዋን መቃጠል ሲያይ አንድ ነገር ማድረግ እንዳለበት አሰበና የከተማዋን ህዝብ ጌይ ሐምቡርጢ (የሀረር እምብርት) በሚባለው አካባቢ ለስብሰባ ጠራ። ከዚያምእንደዚህ ዓይነቱ ድንገተኛ ጥቃት ከተማችንን እንዳያጠፋት ለወደፊቱ ምን ማድረግ አለብን? የሚል ጥያቄ አቀረበ።
   እያንዳንዱ የስብሰባ ተሳታፊ የመሰለውን ተናገረ። አንዳንዶች የከተማዋን በቃ በእጥፍ መጨመር ይበጃል የሚል አስተያየት ሰጡ። ከፊሉም በርካታ መድፎችን ገዝተን በከተማዋ ዙሪያ ብናስቀምጣቸው ይሻላል አሉ። ይሁንና እነዚህ ሁሉ ለአሚር ኑር አልጣሙትም። በመጨረሻም ሸሪፍ አይደሩስ የሚባል ሰው ተነስቶ ከተማዋ ዙሪያ የግንብ አጥር ብንገባ ይሻላል በማለት ተናገረ። አሚር ኑርም በዚህኛው አስተያየት ስምምነቱን በመግለጽ ሁሉም የከተማዋ ነዋሪ ለሃሳቡ ተፈጻሚነት እንዲረባረብ ተዕዛዝ አስተላለፈ። በዚህም መነሻነት ዛሬ ጁገል (ጀጎል) የሚባለው የከተማዋ ግንብ ተወለደ።
  *****  *****  *****
  አሚር ኑር ጁገልን ያስገነባበት ዘዴ በሽማግሌዎች አንደበት ሲነገር በጣም ያስደምማል። በዚህ ላይ የሀረር ከተማ ታሪክ አዋቂዎች ያጫወቱኝን ወግ ከታች አወጋችኋለሁ። ወደዚያ ከመግባቴ በፊት ደግሞ ጁገል የማንንም አድናቆት የሚስብበትን አንዳንድ ውብ ገጽታዎቹን ዘርዘር ላድርግላችሁ፡፡
   ጁገል በሌሎች ስፍራዎች ከምናውቀው ማንኛውም ግንብ ጋር የማይመሳሰል መሆኑ የመጀመሪያው አስደናቂ ገጽታው ነው፡፡ ንድፉም ሆነ ኪነ-ህንጻው በየትኛውም ሀገር ካለ ተነጻጻሪ ግንባታ ጋር አይመሳሰልም፡፡ በሁለተኛ ደረጃም ጁገል ሙሉ በሙሉ ሀገር በቀል (domestic) ግብአቶችን ብቻ በመጠቀም የተሰራ መሆኑም ያስደንቃል፡፡ ከውጪ ሀገር የመጣ ብረትም ሆነ አርማታ፣ ሲሚንቶም ሆነ ገረጋንቲ  አይታይበትም (በምዕራባዊ ክፍሉ ላይ ጣሊያኖች በከፊሉ ከሰሩት የማሰማመሪያ ስራ በስተቀር)።
  ሶስተኛው ደግሞ የጭቃው ጉዳይ ነው፡፡ በጭቃና በድንጋይ ብቻ የተገነባ ግንብ በዝናብና በፀሀይ ሐሩር እንዳይፈራርስ የማጠናከሪያ ድጋፍ ይሻል፡፡ ቢያንስ ቢያንስ ተለስኖ በአሸዋ ይገረፋል፡፡ ጁገል ግን ልስንም ሆነ ግርፍ ሳይኖረው እስከ ዘመናችን ድረስ ቆይቷል (ከዚህ ጀርባ ያለውን ሚስጢር ከወደታች ትረዳላችሁ)።
  ጁገል በግንባታ ዘመኑ (16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ) የነበረውን የምህንድስና ዕውቀት የሚናገር መሆኑም አራተኛው አስደናቂ ገጽታው ነው። ይህንን ለመረዳት ካሻችሁ ግንቡን በአትኩሮት ማየት ይጠበቅባችኋል፡፡ ለዚህም አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ፡፡
   ጁገል የተገነባው ለጥ ባለ (ሜዳማ) መሬት ላይ አይደለም፡፡ ግንቡን መሀል ለመሀል ሰንጥቆ ከሚያልፈውና አሚር ኡጋ (የአሚር መንገድ) ከሚባለው ጎዳና ወዲያና ወዲህ ያለው የጁገል ውስጣዊ ከተማ በሙሉ አቀበትና ቁልቁለት ነው፡፡ በግንቡ ውስጥ ያሉት ቤቶችና መንገዶችም በዚህ ወጣ ገባ መሬት ላይ ነው የተደረደሩት፡፡ ታዲያ ከፍታውን ስትወጡና ስትወርዱ ዝናብ በሚጥልበት ወቅት የሚወርደው ጎርፍ ከግንቡ ውስጥ እንዴት ይወጣ ይሆን? የሚል ጥያቄ በአእምሮአችሁ መመላለሱ አይቀርም፡፡ የዚህን ጥያቄ ምላሽ በፍጥነት ማግኘት ካሻችሁ ግንቡን ከውጪ በኩል ማሰስ ይጠበቅባችኋል፡፡ ይህንን ወስናችሁ አሰሳችሁን በምታካሄዱበት ወቅት በጥቂት ሜትሮች የተራራቁ ቀዳዳዎችን ከግንቡ የታችኛው ጠርዝ ስር ትመለከታላችሁ። ቀዳዳዎቹ በክረምትም ሆነ በበጋ ፍሳሽ ስለማይታጣባቸው አገልግሎታቸውን ለማወቅ ነጋሪ አያሻችሁም፡፡ 
  አዎን! ከጁገል የሚፈሰውን ጎርፍና ከየቤቱ የሚወጣውን እጣቢ የሚያስወግዱት እነኝህ ቀዳዳዎች ናቸው፡፡ ሀረሪዎች ቀዳዳዎቹን ወራበ ኑዱል በማለት ይጠሯቸዋል፡፡ የጅብ ቀዳዳ እንደማለት ነው፡፡ ከጅብ ጋር ምን አገናኛቸውና ነው እንዲህ የተባሉት? ማለታችሁ አይቀርም መቼስ! እኔም ስያሜውን ስሰማ ግርታን ፈጥሮብኝ ነበር፡፡
   ሀረሪ ወዳጆቼ እንዳጫወቱኝና በዶ/ር ካሚላ ጊብ ከተዘጋጀው ጥናታዊ ጽሁፍ እንደተረዳሁት በአንድ ወቅት ጅቦች በነዚህ ቀዳዳዎች ወደ ጁገል ይገቡና አሰስ ገሰሱን ይለቃቅሙ ነበር፡፡ በዚህ ዘመን በቀዳዳዎቹ ወደ ጁገል የሚገባ  ወራባ (ጅብ) ባይኖርም የቀዳዳዎቹ ስም አልተቀየረም፡፡  
*****  *****  *****
 አሁን ከላይ የጠቀስኩትን የጁገል ግንባታ ጥበብ በትንሹ ላጫውታችሁ፡፡
  ጁገል የተገነባበት የድንጋይ አይነት "ሐሺ ኡን" ይባላል፡፡ ይህም በአማርኛ ቋንቋ የበሃ ድንጋይ ተብሎ የሚጠራው ነው፡፡ የሀረሪ  ሽማግሌዎች ሐሺ ኡን በጣም ቀለል ያለ በመሆኑ ለግንባታው እንደተመረጠ ያስረዳሉ፡፡ ይህም ሲባል ግንቡ ከተገነባ በኋላ ግድግዳው ሚዛኑን መጠበቅ አቅቶት እንዳይወድቅ ይታደገዋል ለማለት ነው፡፡
   ግንቡ የተገነባባቸው ድንጋዮች በመጠናቸው ተነባብረዋል፡፡ ማለትም ወደ ግንቡ መሰረት ተጠግተው ያሉት ድንጋዮች ተለቅ ይላሉ፡፡ የግንቡ ከፍታ ሲጨምር የድንጋዮቹ መጠንም እያነሰ ይሄዳል፡፡ በሁለት ትልልቅ ድንጋዮች መካከል ያለ ማንኛውም ክፍተት በአነስተኛ (ቁርጥራጭ) ድንጋዮች ተከድኗል:: ግንቡን ስትጠጉት ከድንጋይ በተጨማሪ የጣውላ ግንዲላዎች በድንጋዮቹ መካከል ተዘርግተው ትመለከታላችሁ። የሀረሪ ምሁራንና ሽማግሌዎች እንደሚናገሩት እነዚህ ጣውላዎች የግንቡን ውሃ ልክ የማስጠበቅ ሚና አላቸው።
   ከላይ እንደገለጽኩት ድንጋዮቹ በጭቃ ብቻ ነው የተጣበቁት፡፡ ጭቃው ግን ተራ ጭቃ እንዳይመስላችሁ፡፡ ይህንን መጽሐፍ በምጽፍበት ወቅት ትልቅ የመረጃ ምንጭ ሆነው የረዱኝ የሀረሪ ባህልና ታሪክ አዋቂ አቶ አብዱሰመድ ኢድሪስ እንደነገሩኝ ጭቃው ለሁለት ወራት እንዲብላላ ተደርጓል።
   ጭቃው የተዘጋጀበትን የአፈር ዓይነት ስታዩት በብዙ አካባቢዎች በስፋት የሚታወቀው ቀይ (መረሬ) አፈር ሊመስላችሁ ይችላል፡፡ አቶ አብዱሰመድ እንዳጫወቱኝ ይህኛው (ጁገል የተገነባበት) የአፈር አይነት ጀጀባ ይባላል። ግንቡ ተገንብቶ ካበቃ በኋላም የላይኛው ጠርዙ በራሳ በተሰኘ ሌላ የአፈር አይነት ተደምድሟል፡፡ ይህም የተደረገው በራሳ ሁለት ጥቅሞች ስላሉት ነው፡፡
   አንደኛ በራሳ አንዳች ነገር ቢዘራበት አያበቅልም። በመሆኑም ወፍ ዘራሽ አረምም ሆነ ሳር በግንቡ ጫፍ ላይ እየበቀለ ግንቡን ለጉዳት የሚዳርግበት ዕድል አነስተኛ ነው፡፡ ሁለተኛ በራሳ በዝናብ ጊዜ የሚወርደው ውሃ ወደ ውስጥ እየሰረገ በግንቡ ላይ አደጋ እንዳያደርስ ይታደገዋል (አፈሩ ዉሃ አያስተላልፍምና)። ታዲያ ሌሎች አደጋዎችን ለማስቀረትስ ምን ተደርጎ ነበር? በማለት ጠይቄም ነበር፡፡ አቶ አብዱሰመድ ኢድሪስ ጥያቄዬን የመለሱት አንድ ምሳሌ በመውሰድ ነው፡፡
   ሰዎች ለፍተው የገነቡትን ቤትና ሌሎችንም ግንባታዎች ከሚተናኮሉ ፍጡራን መካከል አንዱ ምስጥ ነው፡፡ ይህ ተራ የሚመስለው ትንሽዬ ፍጡር በአፈር የተሰራ ነገር ሲገጥመው በቀላሉ ዶግ አመድ የማድረግ ችሎታን ተክኗል። ታዲያ አቶ ምስጥ ጁገልን ወርሮ አደጋ እንዳያደርስበት የጥንቷ ሀረር ጌይ የግንባታ ሙያተኞች አስደናቂ ዘዴ ነበር የተጠቀሙት፡፡     
   ሽማግሌዎችና ታሪክ አዋቂዎች እንደሚናገሩት ምስጥ በእጅጉ የሚፈራው ዘመሚት (በእንግሊዝኛው አጠራር red ant) የሚባለውን ፍጥረት ነው። ስለዚህ ምስጥን ከጁገል አካባቢ ለማባረር ተመራጩ ዘዴ ዘመሚትን መጥራት ነበር፡፡ ይህንን ለማሳካት የተወሰደው እርምጃም ዘመሚቱ የሚወደውን እርጥብ አጥንት በግንቡ ዙሪያ በብዛት መቅበር ነው፡፡
   የዘመሚት መንጋ አጥንቱን ለመውረር በሚመጣበት ጊዜ የምስጥ መንጋ በስፍራው ሲክለፈለፍ ከታየው አጥንቱን ይተውና በምስጡ ላይ ይዘምታል፡፡ ከምስጦቹ ውስጥ በዘመሚት የተበላው ተበልቶ ከጥቃቱ የተረፈውም እግሬ አውጪኝ ብሎ ይፈረጥጣል። ምን ይሄ ብቻ! ምስጥ የሚባል ፍጥረት ዳግመኛ ወደዚያ አካባቢ ለመምጣት አይቃጣም፡፡
     ሀረሪ ሽማግሌዎች እንደሚናገሩት ይህ ተግባር የአንድ ወቅት ኩነት ብቻ ሳይሆን በተደጋጋሚ ጊዜያት ተፈጽሟል። ግንቡ በተገነባባቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ውስጥ በግንቡ ዙሪያ ፍተሻ ይካሄድና ምስጥ መሳይ ነገር ከተገኘ ከላይ በገለጽኩት መንገድ ዘመሚት ይጠራበት ነበር። ይሁንና ይህ ድርጊት ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ቆሟል። ምክንያቱም ጭቃው በደንብ ድርቅ ብሎ ከጠነከረ በኋላ በምስጥ ይበላል ተብሎ ስለማይታሰብ ነው (ምስጥ አዳዲስ የቤት ግድግዳዎችን እንጂ የድሮ ቤቶችን እንደማያጠቃ ልብ ይሏል)።
*****  *****  *****
   የሀረሩ የጀጎል ግንብ (በሀረሪዎች አጠራር ጁገል) የተሰራበት ጥበብ ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል። በነገራችን ላይ አሚር ኑር ግንቡን አሰርቶ ካጠናቀቀ ከሁለት ዓመታት በኋላ ሞቷል። አሚሩ የሞተው በ1567 ዓ.ል. የአፍሪቃ ቀንድ ሀገራትን በከፍተኛ ሁኔታ ባጠቃው ታላቅ ረሃብና እርሱንም ተከትሎ በተከሰተው ወረርሽኝ ወቅት ነው። በዚያ አስከፊ የችጋር ወቅት ሰው ሰውን እስከ መብላት እንደደረሰ የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ። ይሁንና ዲል ወንበራ (የአሚር ኑር ባለቤት) ከዚያ መቅሰፍት ተርፋ ከአሚሩ በኋላ ለብዙ ዓመት ኖራለች። ከሞተችም በኋላ ከምትወደው ባለቤቷ ከአሚር ኑር አጠገብ ተቀብራለች።
  አሚር ኑር ጥንት ሞቷል። ሆኖም ጁገልን የመሰለ ድንቅ ማስታወሻ ትቶልናል። ይህ ግንብ ዛሬም እንደ ጥንቱ ሳይቀየር አለ። ግርማ ሞገስን ተላብሶ በከተማዋ መሃል ላይ ቀጥ ብሎ ቆሟል። እስከ አሁኑ ደቂቃ ድረስ የአሚር ኑርን ታሪክ ይናገራል።
*****  *****  *****
(አፈንዲ ሙተቂ፡ ሀረር ጌይ-የአስገራሚዋ ከተማ የኢትኖግራፊ ወጎች፡ 2004፡ ገጽ  129-134)

Friday, April 19, 2013

A Treatise on Sheikh Umar Aliyyee Galamsiyyi


Written by: Afendi Muteki

The mosque depicted in this photo is found in my hometown. It was built originally by Sheikh Umar Aliyye Al-Harariyyi Al-Galamsiyyi who lived from about 1880 to 1950 and whom the elders of my town remember as a man of many virtues. He was a preacher, teacher, writer, poet, geographer, historian, humanitarian and traditional healer. He is credited for founding the first Islamic educational center of Gelemso town and the second mosque of the town (the first being that of Aw-Seid which is known only in oral history). His personal charisma and tangible achievements tell you the strength and brilliance of once mighty generation of Islamic scholars and thinkers of our country. On the whole, I definitely say he is one of the few influential persons in history of Galamso town.

Sheikh Umar Aliyye was born around 1880 in Mata-Mura village which is found on 15 kms south of Galamso. It is said that his long career as a religious scholar came to be true in a miraculous way. The elders of Galamso town say that Seikh Ali Jaamii Guutoo, the last Qaalluu (the highest religious priest) of the traditional Caffee Assembly of Oda Bultum and the first Muslim to hold that position, started to invoke Allah around the end of his life in order to get a reliable scholar whom he would assign as a heir to his religious career. One day, elders say, the mother of Sheikh Umar Galamsiyyi came to visit Sheikh Ali Jaamii to seek religious guidance on different matters. Then, she had the young Umar on her back that aged only about 3-5 months. Looking at her infant, the old Sheikh Ali Jaamii said “This boy seems the one we are looking for. He seems to be empowered by Allah to grow to an ideal heir who would continue what we have sown and would achieve our goal. May Allah enlighten him in all suefull knowledge. May Allah make him the one who will benefit the whole people”.  Allah heard Sheikh Ali’s prayer and made the then infant boy one of the instrumental figures in religious history of the whole of Harerghe Highlands.
Sheikh Umar attended most of his Islamic studies in Dawwee district of the former Wallo province. He returned back to Gelemso around 1915 with his favorite and long time friend called Sheikh Muhammad Harar (the tomb of this Sheikh is located at Ciroo/Asbe Teferi town). Sheikh Umar built his “Hadra” (religious compound) at Mata Mura, his birth place and started teaching the people of the area. When Italy invaded the country in 1936, he was promoted to the Qaadii of the former Carcar Awraja (today’s West Harerghe Zone). Some landlords of the area were dissatisfied at his promotion and burned down his “Hadra” killing many of his disciples. He left Mata Mura then and moved to Gelemso town where he built another “Hadra” and his mosque.
He worked as a Qadii of Carcar under the Italians. However, in doing so, he didn’t move in any way to revenge the burning of his Hadra and the killing of his disciples by the rebels. He rather shown an exemplary amnesty for those who attacked him and even, using his position as a Qaadii, he greatly supported the rebels who were fighting to expel out the Italian colonists. For example, when the Italians were going to punish the captured Ethiopian rebels by hanging them in public squares and market places, Sheikh Umar used to intervene, argue with the Italian military officials and convince them to change the death penalty to impressments. He also boldly argued with the Italians and convinced them to increase the wages they were paying to the laborers who were employed at a huge construction site located on 20 kms east of Gelemso. Further, Sheikh Umar Galamsiyyi succeeded to convince the Italians to allow those laborers a monthly work leave in the fasting Month of Ramadan (The laborers were known as “Kulii Faabaa”. The elderly people still call the construction site “Kinteerii”- derived from the Italian “cantiere” which was to mean “construction site” or “construction project”. The project was launched to build a new town which was assumed to be a living place for the Italian settlers planned to be brought in from Southern Italy. Now, the old site turned to a new town called “Waaccuu”).
When the Italians were ousted, the good things he did for Ethiopian prisoners of war during the five years occupation increased his merit in the site of the ruling monarchy, and Emperor Haile-Silasie invited him for an award of patriotism and an honorary title (like “Dajjazmach”, “Fitawrari” etc). But Sheikh Umar Aliyyee declined the invitation saying “We did good things not to please anybody but it is our duty to do so. And we expect our award only from Allah who created us”. Haile Silasie smiled at the response and left the award. But he gave two Gasha (80 acres) of land to Sheikh Umar and the latter accepted it. Throughout his life, the sheikh never used the land as a means to accumulate wealth by subjugating the poor tenants as many landowners of the time were doing; he used it just as an input to support his long career of educating the people. (The land was found in Daro Labu district, and it had a boundary with a famous plot owned by Ras Biruu Wolde- Gebriel, a son of Dajjazmach Wolde-Gebriel Abba Seytan and one of the ministers in the cabinet of Ras Teferi Mekkonen in 1920-1930s. Latter in this essay, you will read an interesting story about an incident occurred around this plot of land).
As a teacher of many disciples, Sheikh Umar Galamsiyyi played a vital role in institutionalizing the ordinary teaching and learning condition which was persistent in Harerghe prior to his time. Through his eloquent speeches, he increased the peoples’ awareness about the importance of education in building a civilized and determined society. He extended the scope of the subjects he taught from purely Islamic fields to other important fields like Geography, Hisaab (Aljebraa), History etc... In order to promote the disciples’ attendance in education, he constructed many houses that served as a residence of his students (most of those houses are still standing).
Many people had attended their education under the tutorship of Sheikh Umar Galamsiyyi. His famous students include Sheikh Bakrii Saphaloo (the inventor of the famous “Saphaloo Alphabet”), Sheikh Muhammad Xullaab (a long time Imam and chief Sheikh of Ciroo town), Mufti Muhammad Saalih (one of the first Oromos to graduate from Al-Azhar University), Sheikh Hassan Aannanoo, Haaji Umar Arboyyee (a well known Sheikh based at a place called Darakkuu), Haji Muhammad Khaliif ( a founder of a well-known religious center at Fal’aanaa town in East Harerghe) and many more. However, in my thought, the most astonishing student of Sheikh Umar Galamsiyyi was a man called “Vaska”.
Who was this Vaska? How could he become a disciple of Sheikh Umar? I will end my essay by sharing what was written once by Professor Girma Yohannes Eyyasu, a grandson of Lij Eyyasu Mikael and a member of the family who eye witnessed incidents that made up the story. The story is taken from an online e-mail correspondence done between a writer called Richard Shaltzer who mentioned in his book about a Russian boy called “Vaska”, and Professor Girma Yohannes Eyyasu who was asking the way he could get the books written by that writer. When Professor Girma wrote his first e-mail, Richard Shaltzer asked him about “Vaska”. Then, Professor Girma replied the following.
 “Dear Richard:
Yes, I heard a lot about Vaska; but people like my grandmother used to tell us about "Baska". The story is as follows; but, as I was reading your book of Bulatovich, I was not thinking about our "Baska the young black FERENJ"( Ferenj means White in Amharic).
Baska, told me my grandmother -was very well known at the court of Ras (and after 1914 King) Mikael of wollo(Father of Lij Iyassu -my Grandfather).King Mikael thought, the young man who spoke the language of the Ferenj, could help him as a translator and teacher for his children. Baska also learned Amharic at the court. King Mikael has also tried to get him a wife from the noble family of Wollo; but Baska rejected and told the king that he was a eunuch. King Mikael was sad about the young man and asked him who did that to him. Baska told the King that happend during his childhood to him and it was an officer of Cherencho the King of Kaffa.
Cherencho was in Prison at that time and King Mikael wanted to punish him for that, but his son Lij Iyassu who was in power at the time(1910-1916) did not accept the idea. After the battle of Segele (between the Shoans and King Mikael in 1916) and after King Mikael was captured by Teferi Makonen (late Haile Sellasie), Baska went to the Province of Hararghe with my grandmother in Cher-Cher district. My grandmother who is the daughter of Dejazmach Woldegebriel and elder sister of Ras Birru owned a very large Land and property there.
She told us that sometimes she was angry with him because he ate meat, eggs or drank milk on wendsdays fraidays which was a taboo to the Christians. At the age of 25 Baska wanted to be a Monk and go to monastery, but he thought he will not success. Baska finally started to write and read arabic, his teacher was Mohammad Ubadin an immigrant from Jemen and a close friend of my grandmother (because he bought a piece of land from her and as an importer he brought her some Pieces of clothes and perfumes).
But on one Friday in the month of may Baska came very late in the afternoon to my grandmother and told her that he came late because he was converted to Islam. My grandmother was near to heart attak as she heard that; she shouted and get mad, but Baska told her that he was not satisfied with his own life and want to serve only "the Almighty".
At the same day he collected his belongings and went to the town called Gelemso; which is about 65 or so Kms away and joined Shaik Umar Ali.
After 10 years my grandmother visited him at Gelemso. The story is interesting. My grandmother and the Shaik had a land dispute which lasted about seven years, before going to the higher court Baska solved the problem at once. He advised both in such a philosophical way that both gave the boarder piece of land to a very poor family who enjoyed it. This piece of land was named by the community as "Baska Land".
This is the story I remember and I think he died some times later and buried there. I have a very old book of our family from Wollo I will check whether the chronist recorded it.
Dr. Girma Iyassu “
(You can get the full story from this link http://www.samizdat.com/menelik.html )

Isn’t it interesting? I came across this story two years ago while I was browsing the internet. I became very eager to know the end of the story and asked members of the family of Sheikh Umar whether they have any knowledge about Vaska. Unfortunately, nobody knows him. The only thing they told me was the location of the vast land that belonged to Sheikh Umar (it was found in Daro Labu district as I said in the above section). I will try to investigate the story in detail and find out the final fate of Vaska. Insha Allah!!
Sheikh Umar Aliyye married four women throughout his life, and he had many offsprings including the hero called Mohammed Zakir (Meyraa). The biography of Sheikh Umar Aliyye was written by his student I aforementioned as Hajji Umar Arboyyee under a title “Jawahirul Zdahabil Ahmar Fi Manaqibil Ustazil Akbar Sheikh Umar Galamsiyyi”.
 Afendi Muteki
April 20, 2013
Harar
Notes:
1.      In the will of the Almighty (Allah), I planned to enlarge this short essay and include it in one of my future books titled “Gelemso: Its People, Its History and Its Heroes”. I need your feedback and corrections (especially I expected corrections and extra information from those who belong to the family of Sheikh Umar)
2.      I know that during his life time, Sheikh Umar Aliyye produced certain geographical maps, measuring tools, globes, astronomical sketches and tables etc… I will try to bring their photo if I can get any.

Monday, April 1, 2013

የገለምሶው “አቦ ደርጂ” ጨዋታዎች


    ጸሓፊ፡- አፈንዲ ሙተቂ
 
በተወለድኩባት ከተማ ስማቸው ገኖ ከሚወራላቸው ጥቂት ሰዎች መካከል አንዱ ናቸው። እኝህ ሰው የናጠጠ ቱጃር ወይንም የመሬት ከበርቴ አልነበሩም። “የሼኽ እገሌ ቤተሰብ አባል” ወይም “የሸሪፍ እገሌ ዝሪያ” የሚባሉ አይነትም አይደሉም። ይሁንና የከተማችን ተወላጆች ከመሬት ከበርቴም ሆነ ከናጠጠ ቱጃር በላይ ያስታዉሷቸዋል። በተለይ ከእርሳቸው ጋር በጉርብትናና በአጥቢያ (ሰፈር) የምናዛመድ ሰዎች ዘወትር አንዘነጋቸውም።
      ደርጂ ሙሳ ይባላሉ። ተወላጅነታቸው በጭሮ (ዐሰበ ተፈሪ) ቢሆንም ከጣሊያን ዘመን ጀምሮ ህይወታቸው እስክታልፍ ድረስ በገለምሶ ከተማ ነው የኖሩት። በቀልደኝነታቸውና በጨዋታ አዋቂነታቸው የከተማው ሰው በሙሉ ይወዳቸዋል። መከራ በገጠማቸው ጊዜ ከጥቃት ለማምለጥ የሚፈጥሯቸው ብልሀቶችም የብዙዎችን አድናቆት አስገኝተውላቸዋል። በዚህም የተነሳ የከተማችን ነዋሪዎች “አቦ ደርጂ” እያሉ ነው የሚጠሯቸው። (“አቦ” በኦሮምኛ “አባት” እንደማለት ነው። ታዲያ ይህኛው “አቦ” ሲነበብ ጠበቅ ይላል። ላልቶ ከተነበበ ትርጉሙ ይለወጥና “አንተ” እንደማለት ይሆናል)። የ“አቦ ደርጂ” ጨዋታ አዋቂነትና አባ-መላነት ከከተማችንም አልፎ በአጎራባች ከተሞች ጭምር በመናኘቱ በህይወት እያሉ ተረት እስከመሆን ደርሰዋል (ልክ እንደ ጋሼ ስብሃት ማለት ነው)። እነሆ እኔም ከአቦ ደርጂ ጨዋታዎች መካከል ለበረካ ያህል አንዳንዶቹን አጫውታችኋለሁ።
*****  *****  *****
   አንድ ጊዜ ጓድ ሊቀመንበር መንግስቱ ኃይለማርያም በገለምሶ አቅራቢያ ያለችውን “ዴፎ” የተሰኘች አነስተኛ ከተማ ለመጎብኘት እንደሚመጡ ይነገራል። የገለምሶ ህዝብም “ቆራጡ መሪያችን በከተማችን ሲያልፉ ሰላምታ እንድትሰጧቸው” የሚል አስገዳጅ ጥሪ ተላልፎለታል። በጥሪው መሰረትም “አቦ ደርጂ” ለጓድ ሊቀመንበር አብዮታዊ ሰላምታ ለመስጠት ከአካባቢው ሰዎች ጋር በሱቃቸው ፊት ለፊት በሚያልፈው መንገድ ዳር ይቆማሉ። ሆኖም “መንጌ” በተባለው ጊዜ አልደርስ አሉ። ለረጅም ሰዓት መንገድ ዳር መቆሙ ያሰለቻቸው አቦ ደርጂ “ለአንድ ሰው ብለው ስራ ያስፈቱናል፤ ይህንን ሁሉ ህዝብ መንገድ ዳር ለረጅም ሰዓት ማስቆም አግባብ ነው? ስራ ፈት ካድሬ ሁሉ!” እያሉ ማጉተምተም ጀመሩ። ለካስ አንድ ነጭ ለባሽ (ሲቪል ለባሽ የደህንነት ሰው) ከአጠገባቸው ቆሞ ይሰማቸው ኖሯል? ወዲያውኑ ፖሊሶችን ጠርቶ “እርምጃ ይወሰድባቸው” ከሚል ትዕዛዝ ጋር ወደ አውራጃው ፖሊስ ጣቢያ አስወሰዳቸው።
    የአውራጃው ፖሊስ አዛዥም ከፊቱ የቆሙትን አቦ ደርጂ እያየ “እህስ ሽሜ! ቅድም ምን ስትል ነበር?” በማለት ይጠይቃቸዋል። ነገሩ ክፉ አደጋ ሊያስከትልባቸው እንደሚችል አስቀድሞ የተረዱት አቦ ደርጂም “አሃ! ጫቱን ነው?” አንተ ካልክ እሺ! አንተ እንደፈለግክ አደርጋለሁ!” በማለት በአፋቸው የሚያመነዥኩትን ጫት በፊታቸው ላይ ይለቀልቁት ገቡ። ነገሩ ያስደነገጠው የፖሊስ አዛዥ “አንተ ሰውዬ! ምን እያደረግክ ነው? ማን ነው በጫት ፊትህን አበላሸው ያለህ?” በማለት ደነፋ። አቦ ደርጂም ምንም ሳይሸበሩ “አንተ ካልክ አደርገዋለሁ! ምን ገዶኝ! ይኼው አደርገዋለሁ!” በማለት የታጠቁትን ሽርጥ ፈትተው ጣሉትና ከወገብ በታች ራቁታቸውን ቆሙ። ይሄኔ አዛዡ በጣም ተደናገረና በአቅራቢያው የነበረውን አንድ ፖሊስ ጠርቶ “አንተ ወታደር! ሽማግሌው እብድ ነው! ቶሎ ከዚህ አስወጣው” በማለት ትዕዛዝ ሰጠ። አቦ ደርጂም በዚያች በቅጽበት በፈጠሩት መላ ህይወታቸውን ከሞት አተረፏት።
*****  *****  *****
    በደርግ ውድቀት ማግስት አቦ ደርጂ አዲስ ሚስት አገቡ። ይህች ሚስት የደም ግባቷ በጣም የተወራላት ከመሆኗም በላይ በእድሜዋ በሀያዎቹ መጨረሻ ገደማ የምትገኝ ነበረች። እናም ሽማግሌው አቦ ደርጂ ወጣት ሚስት ማግባታቸው በመላው የገለምሶ መንደሮች መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በነገሩ የተገረሙት አንድ ጎልማሳም ወደ አቦ ደርጂ ዘንድ ይሄዱና “አንተ ለራስ ጥርስ የለህ፣ አርጅተሃል፣ ምን ልሁን ብለህ ነው በስተ እርጅና ሚስት የምታገባው?” በማለት ይጠይቁአቸዋል። አቦ ደርጂ በነገሩ እየሳቁ “ወይ ጉድ! እናንተ ጥርሰ በረዶዎች ሚስቶቻችሁን በጥርሶቻችሁ ነው የምትነካክሱት እንዴ?” በማለት ጥያቄውን በጥያቄ መለሱት።
*****  *****  *****
   በዚህች ወጣት ሚስታቸው ሳቢያ ነገር የበዛባቸው አባ ደርጂ ሌሎች ሰዎች ሚስቴን ሊያስኮበልሉብኝ ይችላሉ የሚል ፍራቻ አድሮባቸው ነበር ይባላል። ታዲያ ነጅብ ኢድሪስ የሚባለው የከተማችን ነጋዴ በዚያው ሰሞን የደረሰበትን አንድ ነገር እንደሚከተለው አጫውቶኝ ነበር።
   አቦ ደርጂ ለቅሶ (ታዚያ) ለመድረስ ራቅ ወዳለ ሰፈር ይሄዱና ይመሽባቸዋል። ወደቤታቸው ለመመለስ ቢፈልጉም የጨለማው ነገር የሽማግሌ አይናቸውን የማይመጥን ሆኖ ያገኙታል። ስለዚህ ለታዚያ (ለቅሶ) በተተከለው ድንኳን ውስጥ ያሉትን ሰዎች ወደ ቤታቸው እንዲያደርሷቸው ትብብር ይጠይቃሉ። በዚህ መሰረትም ከላይ የጠቀስኩት ነጅብ ኢድሪስ ፈቃደኛ ሆኖ እስከቤታቸው ድረስ ሊወስዳቸው ይነሳል።
   ሁለቱ ሰዎች መንገዳቸውን ጀመሩ። ነጅብ ባትሪውን ለአቦ ደርጂ ሰጥቶ ለራሱ ፊት ቀድሞ መጓዝ ጀመረ። እናም በአጭር ጊዜ ውስጥ ከቤታቸው አደረሳቸው። ነጅብ መንገዱን ሳይስት ከቤታቸው መድረሱ ያስገረማቸው አቦ ደርጂ ምስጋናቸውን ካቀረቡለት በኋላ “Ammoo Kharaa mana khiyyaa khana akkamitti akkati haffazde?” (“ግን ወደቤቴ የሚያደርሰውን መንገድ እንዴት ነው እንዲህ የሸመደድከው?”) በማለት ከልቡ አሳቁት።
    አቦ ደርጂ ወጣት ሚስት ከቤት ውስጥ እንዳላቸው የሚያውቀው ነጅብ “ኖራ ነጭ ነው” እንዲሉት አይጠብቅም። ለዚህም ነው በነገሩ ከአንጀቱ የሳቀው (እኔም ከአቦ ደርጂ ጨዋታዎች ሁሉ በጣም ያሳቀኝ ይህኛው ነው)።
******************
     በደርግ ጊዜ ሁሉም ጎልማሶች መሰረተ ትምህርት እንዲማሩ በሚያስገድደው ደንብ መሰረት አቦ ደርጂም ለትምህርት ገብተው ነበር። ግን የትምህርቱ አሰልቺነት በወቅቱ ከነበሩበት የኑሮ ሁኔታ ጋር ተዳምሮ አቦ ደርጂን ያነጫንጫቸው ገባ (በወቅቱ የመጀመሪያ ባለቤታቸውን በሞት የተነጠቁት አቦ ደርጂ ልጆቻቸውን እንደ እናትም እንደ አባትም ሆነው ያሳድጉ ነበር)። በዚህም የተነሳ አንድ ሰበብ ፈጥረው ከትምህርቱ ገበታ ለመጥፋት ወሰኑ። በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉም ትምህርቱን የሚያስተምረው አስተማሪ አንድ ቀን የሂሳብ ጥያቄ ያቀርብላቸዋል።
“አቦ ደርጂ፣ አንድ ሲቀነስ አንድ ስንት ነው የሚሆነው?”
“እኔ ስለመቀነስ አላውቅም፤ መደመር ጠይቀኝ”
“እንዴት አያውቁም? ነጋዴ አይደሉም?”
“ነጋዴ ብሆንም ስለመቀነስ አላውቅም”
 
   ነገሩ ግራ የገባው አስተማሪ በምሳሌ ማስረዳት አማረውና “ለምሳሌ አቦ ደርጂ፤ አንድ ሙዝ አለኝ እንበል። እርሱን ብበላው ምን ያህል ይቀረኛል?” በማለት ይጠይቃል። አቦ ደርጂም “አይ አስተማሪው! ልጣጩ እንጂ ምኑ ነው የሚቀረው” የሚል ምላሽ ሰጡት። ይህንን የሰሙት በክፍሉ ውስጥ የነበሩት ጎልማሳ ተማሪዎች በሙሉ በሳቅ ያውካካሉ። አስተማሪው ግን በነገሩ ይናደድና ቂም ቢጤ ይቋጥራል።
   በሌላ ጊዜ ደግሞ አስተማሪው አንድ ስነ-ግጥም በጥቁር ሰሌዳው ላይ ይጽፍና ተማሪዎቹን “በደብተራችሁ ገልብጣችሁ አሳዩኝ” በማለት ያዛቸዋል። አቦ ደርጂም በደብተራቸው ላይ ምንነቱ የማይገባ ነገር ሙጭርጭር አድርገው ይጽፉና ለማሳረም አስተማሪው ዘንድ ይወስዱታል። ታዲያ መምህሩ ነገሩን ሲያይ በአቦ ደርጂ አድራጎት እጅግ ተደንቆ “ይህ ደሞ ምንድነው?” በማለት ይጠይቃቸዋል። እርሳቸውም “ጽሁፍ ነው” በማለት በአጭሩ ይመልሳሉ። መምህሩም “የምን ጽሁፍ ነው? እንዴትስ ተደርጎ ነው የሚነበበው?” በማለት መልሶ ሲጠይቅ አቦ ደርጂም ዘና በማለት “አስተማሪው! ጽሁፉን ከቻልክ አንብበው፤ ካልቻልክ ለበላይ አካል አስተላልፈው፤ ራስህን ብዙም አታስጨንቀው” የሚል አብሻቂ መልስ ሰጡት። የአቦ ደርጂ ነገር ያልጣመው አስተማሪ “እርስዎ ትምህርት አይፈልጉም፤ስለሆነም ሁለተኛ እዚህ እንዳይመጡብኝ” በማለት አሰናበታቸው። በዚህም ብልሃት አቦ ደርጂ ከመሰረተ ትምህርቱ መድረክ ተለዩ።
     *****     *****   *****  
  አቦ ደርጂ ዘወትር የሚታወሱበት አንዱ ባህሪ ድፍረታቸው ነው። አንደበታቸው እንደ ብዙዎቻችን በይሉኝታ ገመድ የተሸበበ ስላልሆነ ያልጣማቸውን ነገር ፊት ለፊት ከመቃወም ወደ ኋላ አይሉም። ታዲያ እምቢ ባይነታቸው በደረቅ ቃላት የተደረተ አይደለም። እውነትን በሰፊው ይገልጻል። አንዳንዴ ደግሞ በአዝናኝነቱ የሁል ጊዜ ተጠቃሽ ሆኖ ይኖራል። ለዚህም ሁለት አብነቶችን ልስጣችሁ።
   ኢሕአዴግ ሀገሪቱን ከተቆጣጠረ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ነው። ስለ አዲሱ ስርዓት አካሄድና ስለዜጎች መብት በሚል በየቀበሌው ህዝባዊ ስብሰባ ይካሄድ ነበር። አቦ ደርጂ በታደሙበት አንድ ስብሰባ ደግሞ የመድረኩ መሪ አደም አብደላ (በቅጽል ስሙ “ጉመ ከፈል”) የሚባል የምዕራብ ሀረርጌ ዞን አስተዳዳሪ ነው። ታዲያ “ጉመ ከፈል” ስብሰባውን እየመራ ሳለ በአዳራሹ የመጀመሪያ ረድፍ ላይ ወደ ተቀመጡት አቦ ደርጂ እያየ እንዲህ አላቸው።
    “አባቴ፣ እርስዎ ትልቅ ሰው ነዎት፤ ቢያንስ ሶስት መንግስታትን አይተዋል። እስቲ የኃይለ ስላሴን፣ የደርግንና የአሁኑን መንግስት በማነጻጸር ሀሳብዎትን ይስጡኝ።”
አቦ ደርጂም “የእውነት መልስ ነው የምትፈልገው ወይስ ውሸት እንድናገር ነው የምትፈልገው?” አሉ።
    ጉመ-ከፈልም “እውነት ነው እንጂ ውሸት ምን ይሰራልኛል?” አላቸው።
አባ ደርጂም “ጥሩ! ኃይለስላሴ በድንቁርና ፈጀን። ከባላባት ልጆች በስተቀር የኛ ልጆች መማር አይችሉም ነበር። ደርግ ደግሞ “ቀይ ሽብር” እና “አብዮታዊ ዘመቻ” እያለ ልጆቻችንን ጨረሰብን። ስለአሁኑ መንግስት ግን ከወረደ በኋላ ብትጠይቀኝ ይሻላል” በማለት የዞኑን አስተዳዳሪና በአዳራሹ የነበረውን ህዝብ በሳቅ አፈረሱ።
     *****     *****   *****  
    ዝናብ በጠፋበት በአንድ ወቅት ደግሞ ህዝቡ በመስጊድ ውስጥ ከሰላት (ስግደት) በኋላ ፈጣሪውን ይለማምናል። የመስጊዱ ኢማም ከተቀመጡበት ተነስተው ህዝቡ ቀንም ሆነ ማታ ፈጣሪውን መማጸኑን እንዳይተው አሳሰቡ። በመስጊዱ የነበረውም መላው ህዝብ ይሁንታውን ገለጸ። አቦ ደርጂ ግን “የምን ዝናብ ነው የምታወሩት? አይሆንም! እስቲ ይዝነብ!” በማለት ተቃውሞአቸውን አሰሙ። በዚህም የተነሳ በመስጊዱ የነበረው ህዝብ ተደናገጠ።
     ኢማሙ ግን “ቆዩ! ረጋ በሉ!” ካሉ በኋላ አቦ ደርጂ እንደዚያ ያሉበትን ምክንያት እንዲያስረዱ ጠየቁአቸው። እርሳቸውም “አምና የነፈሰው ሀይለኛ ነፋስ የቤቴን ጣሪያ ነቃቅሎት እንዳልነበረ አድርጎታል። ዘንድሮ ዝናቡ ከደገመኝ ደግሞ እኔና ልጆቼ የምንደርስበት ቦታ አጣን ማለት ነው። ስለዚህም ነው አይዝነብ ያልኩት” በማለት ተናገሩ።
ይህንን የሰሙት የመስጊዱ ኢማም ወደ ህዝቡ በመዞር “አያችሁ ሰዎች! ፈጣሪ የሚቀጣን እኮ ሀጢአታችን ስለበዛ ነው። እንደ አቦ ደርጂ ያሉ ሽማግሌዎችን ስለማናስታውስ ዝናቡም ይጠፋብናል። አሁን በአስቸኳይ ለአቦ ደርጂ ጣሪያ ጉዳይ መፍትሔ መፈለግ አለብን” አሉ። ወዲያው በመስጊዱ የነበረው አንድ ነጋዴ “የአቦ ደርጂን ጣሪያ እኔ ራሴ ነገውኑ አሰራዋለሁ” በማለት ሀላፊነት ወሰደ። ቃሉንም በሚቀጥለው ቀን ተግባራዊ አደረገ።
    እንግዲህ የአቦ ደርጂ ድፍረት እንዲህ ነው። በመስጊድም ውስጥ ቢሆን የተሰማቸውን ከመናገር ወደ ኋላ አይሉም። ሌላ ሰው ቢሆን ኖሮ ይሉኝታ ይዞት በዝምታው ይጸናል። ነገር ግን ይሉኝታ በሁሉም ቦታ አይሰራም። በተለይ መጠለያን በመሰለ መሰረታዊ ነገር ላይ አደጋ የሚጋርጥ ሁኔታ ሲፈጠር በዝምታ ማለፍ አግባብነት የለውም።
     *****     *****   *****  
   አንድ ጊዜ አቦ ደርጂ ታመሙ። በአካባቢው የነበርን ሰዎች ተሰባስበን ወደ ሀኪም ቤት ወሰድናቸው። ተረኛ ሀኪሙም ከመረመራቸው በኋላ መርፌ አዘዘላቸው። መርፌውን የሚወጋቸው ነርስም መጣ። መድኃኒቱንም ከሲሪንጅ ውስጥ ጨምሮ በታፋቸው ላይ ሰካ። መርፌው ግን በጣም ስላሳመማቸው አቦ ደርጂ በሀይለኛ ሁኔታ ተቆጡ፤ ነርሱንም እንዲህ አሉት፣ “አንተ! በኔ ላይ እየተለማመድክ ነው እንዴ?”
ከአሁን አሁን አንድ ነገር ይናገሩ ይሆናል ብለን የምንጠብቀው ሰዎችም ሀኪም ቤቱን በሳቅ ሞላነው።
     *****     *****   *****  
     የአቦ ደርጂ ልጅ ካገባ አንድ ሶስት ወር ሆኖታል። በዚያው ሰሞን የተወሰንን ሰዎች ከርሳቸው ጋር በመንገድ ላይ ተገናኘን። አንዱ ጓደኛችንም ወሬ ለመጀመር ያህል “አቦ ደርጂ! ልጅዎት እኮ አገባ!” አላቸው። እርሳቸውም ቀድመው የሰሙት ነገር በመሆኑ ቀዝቀዝ ያለ መልስ ሰጡት።  ሌላው ጓዳችን ደግሞ “ኧረ! እኔ እንዲያውም ወለደ ሲሉ ነው የሰማሁት” አላቸው። ይሄኔ አቦ ደርጂ “Mucaan khiyya baatii sadii kheessatti yoo dhale intalti inni fuudhe “Bukkurii” jechuudha gaa!” (“ልጄ በሶስት ወሩ የሚወልድ ከሆነ “ቡኩሪ” ነው ያገባው ማለት ነዋ!” በማለት ማንም ያልጠበቀውን ንግግር ተናገሩ። አቤት የዚያኔ የሳቅነው ሳቅ! እስካሁን ድረስ አይረሳኝም።
   (ማስታወሻ፡- ቡኩሪ የሀረርጌ ገበሬዎች በበልግ ወቅት የሚዘሩት የበቆሎ ዝርያ ነው። ይህ የበቆሎ ዓይነት ከሶስት ወራት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ለምግብነት ይደርሳል። አቦ ደርጂም “ልጄ ያገባት ሚስት በሶስት ወራት ውስጥ ከወለደች ልክ እንደ ቡኩሪ በአጭር ጊዜ የምታፈራ ዘር መሆን አለባት” ማለታቸው ነው።)
     *****     *****   *****  
    የሀብታም ቤተሰብ ተብለው ከሚጠቀሱት አንዱ ነው። የዚህ ቤተሰብ ሰዎች ልጃቸውን ለመዳር ያስቡና በአካባቢው በሚታወቀው ባህል መሰረት “ጂማ” (የሽምግልና ጫት”) ለማስገባት ይወስናሉ። አቦ ደርጂንም ለሽምግልና ወደ ልጅቷ ቤት በሚላከው ቡድን ውስጥ ለማካተት በማሰብ ያማክሯቸዋል። አቦ ደርጂ ግን በነገሩ ከት ብለው በመሳቅ “እኛ ዘወትር ጫታችንን እየቃምን ነው፤ አልሐምዱሊላህ! ፈጣሪ ለበርጫ የሚሆነን ያህል ነፍጎን አያውቅም። ባይሆን እኛን ድኩማኑን መጥራት ያለባችሁ ሰንጋ ተጥሎ ጥብስና ክትፎው በሚደረደርበት ቀን ነው፤ አደራ ያኔ እንዳትረሱኝ!” አሏቸው። እውነትና ብስለት የሞላበት ንግግር ! በድህነት የሚኖሩትን ወገኖች ”ሀጃ” (ጉዳይ) ሲይዛቸው ብቻ ለሚያስታውሱት የሀብታም ከንቱዎች የሚገባ መልስ ነው። 
   በአንድ ወቅት እንዲህ ዓይነቱ ነገር በከተማችን ውስጥ በስፋት ይታይ ነበር። ሀብታም የሚባል ሰው ድሃውን የሚያስታውሰው ጉዳይ ሲይዘው ብቻ ነው። በሀብታም ሰርግ ላይ የሚታደሙትም ሀብት ያላቸው ወገኖች ብቻ ናቸው። አባ ደርጂም በጊዜው የተቃወሙት እንዲህ አይነቱን ኢ-ሞራላዊ ድርጊት ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የድሮው ብልሹ ስርዓት እየቀረ ነው። ወደፊት የበለጠ መሻሻል ይታያል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
     *****     *****   *****  
   የገለምሶው አቦ ደርጂ ጨዋታዎች ብዙ ናቸው። እኔ ያልሰማኋቸው በርካታ ወጎች እንዳሉም አምናለሁ። ለወደፊቱ ሁሉንም በማሰባሰብ ለአንባቢያን ለማቅረብ እሞክራለሁ። ለአሁኑ ግን በዚሁ ይብቃኝ። ፈጣሪ የአቦ ደርጂን ነፍስ በጀንነት ያኑራት!
  ሰላም!
አፈንዲ ሙተቂ
መጋቢት 11/2005 ዓ.ል.
ሀረር