Monday, January 5, 2015

ቅዱስ ቁርኣን በአማርኛ ሲተረጎም




ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
-----
ቅዱስ ቁርኣን በአማርኛ እንዲተረጎም ትዕዛዝ ያስተላለፉት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ነበሩ፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ትዕዛዙን የሰጡት ወዳጆቻቸው ከነበሩት የግብጹ መሪ ጀማል አብዱናሲር እና የሳዑዲ ዐረቢያው ንጉሥ ፈይሰል ቢን ዐብዱል አዚዝ “ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች እምነታቸውን በራሳቸው ቋንቋ እንዲማሩ ሊደረግ ይገባል” የሚል ጫና ስለመጣባቸው እንጂ በራሳቸው ተነሳሽነት አልነበረም፡፡ ቢሆንም ንጉሡ እንዲህ ዓይነት ስራዎች መፈጸማቸውን ቀርቶ መታሰባቸውን እንኳ እንደ ድፍረት ይቆጥሩ የነበሩትን የወግ አጥባቂ መኳንንትና መሳፍንትን ተቃውሞ ሳይፈሩ ስራው እንዲጀመር በመወሰናቸው ሊመሰገኑ ይገባል፡፡

ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ትእዛዙን ያስተላለፉት ሐምሌ 18/1958 በተጻፈ ደብዳቤ ነበር፡፡ የንጉሡን ደብዳቤ በመንተራሰስ ስራው እንዲጀመር ያደረጉት ደግሞ በወቅቱ የትምህርት ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ምናሴ ሃይሌ ናቸው፡፡ ዶ/ር ምናሴ በተርጓሚነት የመረጡት ከአል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ ተመርቀው በማስታወቂያ ሚኒስቴር ስር የሚታተመው የ“አል-ዐለም” ጋዜጣ ምክትል ዋና አዘጋጅ በመሆን ይሰሩ የነበሩትን ሐጂ በሺር ዳውድን ነው (ሐጂ በሺር እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ የተገነባው ትልቅ መስጂድ ኢማም እንደነበሩ አውቃለሁ፤ በሚዲያም አንድ ሁለቴ አይቼአቸኋለሁ፤ አሁን በህይወት ይኖሩ ይሆን?… እስቲ መረጃ ካላችሁ አቀብሉን)፡፡

ሐጂ በሽር ከዶ/ር ምናሴ የተሰጣቸውን አመራር በግርድፉ አልተቀበሉትም፡፡ “ቁርኣንን መተርጎም ሌሎች መጽሐፍትን እንደ መተርጎም ተደርጎ ሊታይ አይገባም፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ኮሚቴ ተዋቅሮ ኮሚቴው በሚሰጠው መመሪያ መሰረት ነው መሰራት ያለበት” የሚል ምላሽ ነበር የሰጡት፡፡ አባባላቸው ተቀባይነት በማግኘቱም የቁርኣን ትርጉም ኮሚቴው ተዋቀረ፡፡ ከሀገር አቀፉ ኮሚቴ አባላት መካከል እንደርሳቸው የአል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ የነበሩት ሼኽ ዓብዱል ከሪም ኑርሑሴን እና ሙሴ ሰሊም ቡሽቅራ ይጠቀሳሉ፡፡

  ኮሚቴው የትርጉሙን ስራ በብቃት ማከናወን የሚችሉ ዓሊሞችን ማፈላለግ ጀመረ፡፡ በወቅቱ ትልቁ ችግር የነበረው በእስላማዊ እውቀትም ሆነ በዓለማዊ ትምህርቱ ብቁ የሆነ ዓሊም ማግኘት ነበር፡፡ በተለይም አማርኛ ቋንቋን አስተካክሎ ከመጻፍ ጀምሮ የቋንቋውን የሰዋስው እና የስነ-ልሳን ህግጋትን ጠንቅቆ የሚያውቅ ዓሊም ማግኘቱ አስፈላጊ ነበር፡፡ ብዙዎቹ ዓሊሞቻችን የመጀመሪያውን መስፈርት ቢያሟሉም የኋለኛው ይጎድላቸው ነበር፡፡ ሆኖም ኮሚቴው በሓጂ በሺር ዳውድ ጠቋሚነት ሁለት ሰዎችን አገኘ፡፡ እነርሱም በጊዜው በደሴ ከተማ በሚገኘው የወይዘሮ ስሒን ትምህርት ቤት የሚያስተምሩት ሓጂ ሙሐመድ ሣኒ ሐቢብ እና የሸሪዓ ፍርድ ቤት ዳኛ የነበሩት ሼኽ ሰይድ ሙሐመድ ሳዲቅ ነበሩ፡፡ በዚህ መሰረት ሁለቱ ዓሊሞች ዋና ተርጓሚ ሆነው ስራቸውን ጀመሩ፡፡ ሓጂ በሺር ዳውድ እና ሼኽ ዐብዱል ከሪም ኑርሑሴን ደግሞ ተባባሪ ኤዲተሮች ሆነው እንዲሰሩ ተመደቡ፡፡

ተርጓሚዎቹ ከኤዲተሮቹ ጋር በቅርበት እየሰሩ በአስራ አምስት ወራት ውስጥ ስራቸውን አጠናቀቁት፡፡ ሆኖም ከየክፍለ ሀገሩ የተመረጡ ዑለማ የትርጉሙን ረቂቅ አንብበው የእርማትና የማሻሻያ ሓሳቦችን እንዲሰጡበት ያስፈልጋል የሚል ሃሳብ ተሰነዘረ፡፡ በዚሁ መሰረት የሚከተሉት ታላላቅ ዑለማ ወደ ኮሚቴው ቀርበው ረቂቅ ስራውን በማንበብ ሃሳባቸውን እንዲሰጡበት ተደረገ፡፡

ሼኽ ቡሽረል ከሪም ሙስጠፋ (ከወሎ)
ሓጂ ዩሱፍ ዐብዱራሕማን ገራድ (ከሀረርጌ)
ቃዲ ሙሐመድ ዐብዱራሕማን (ከትግራይ)
ሓጂ አሕመድ ዳለቲ (ከሸዋ)
ሓጂ መንዛረሁ ከቢር ሑሴን (ከአርሲ)

በመጨረሻም ተርጓሚዎቹ ከአምስቱ ዑለማዎች የተሰጡትን አስተያየቶችና ሌሎች የማሻሻያ ሃሳቦችን በመቀበል ረቂቁን አርመው አዘጋጁ፡፡ አሁን በእጃችን ላይ የሚገኘው የቅዱስ ቁርኣን የአማርኛ ትርጉምም በ1961 የመጀመሪያ ወራት ውስጥ ለህትመት በቃ፡፡
-----
ቅዱስ ቁርኣን በአማርኛ የተተረጎመበት ሂደት ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል፡፡ ይሁንና አንዳንድ ጸሐፊዎችና ደራሲዎች ይህንን ታሪክ እንዳሻቸው ሲጽፉት ተመልክተናል፡፡ ለምሳሌ ፕሮፌሰር ሃጋይ ኤልሪችን የመሳሰሉ ፀሐፍት የትርጉም ስራው ባለቤትና መሪ አድርገው የሚጠቅሱት ተርጓሚዎቹ ረቂቁን ከጨረሱ በኋላ በኮሚቴው ጋባዥነት ሃሳባቸውን ከሰጡት አምስት ዑለማ መካከል አንዱ የነበሩትን  ሓጂ ዩሱፍ ዐብዱራሕማንን ነው፡፡ ፕሮፌሰር ኤልሪች ዋነኞቹ ተርጓሚዎቹ ሓጂ ሙሐመድ ሣኒ እና ሼኽ ሰይድ ሙሐመድ ሳዲቅ መሆናቸውን አጥተውት አይደለም ይህንን የሚያደርጉት፡፡ እርሳቸው ዘወትር “አሕባሽ እና ወሃቢያ” እያሉ በሚያቀርቧቸው መጣጥፎች  ውስጥ ከፍተኛ የአትኩሮት ማዕከል አድርገው የቀረጿቸውን ሓጂ ዩሱፍ ዐብዱራሕማንን ለማጥቆር ሲሉ ነው እንዲህ ዓይነት ታሪክ የሚጽፉት፡፡ የሚገርመው ደግሞ ሌሎች ምሁራን ይህንኑ የሃጋይ ኤልሪችን ትረካ እንደ ወረደ ተቀብለው ማስተጋባታቸው ነው፡፡ ለምሳሌ ፕሮፌሰር ፓትሪክ ዴስፕላት የሚባሉት ጀርመናዊ ምሁር በአንድ ጽሑፋቸው እንዲህ ይሉናል፡፡

“Hadj Yusuf became closer to the Ethiopian government and supervised the first official translation of the Quran into Amharic, published in 1961”.

(Patrick Desplat, The Articulation of Religious Identities and their Boundaries in Ethiopia: A Case Study on Harar, Journal of Religions in Africa, Lieden, 2005, pp 497)


  እርግጥ ሓጂ ዩሱፍ ቅዱስ ቁርኣንን የመተርጎም ብቃት ያላቸው ዓሊም ነበሩ፡፡ ከእዉቁ የመዲና ዩኒቨርሲቲ የተመረቁ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ከመሆናቸውም ባሻገር የአማርኛ ቋንቋ እውቀታቸውም ከፍተኛ ነበረ፡፡ በህይወት ሳሉም ለኢትዮጵያን ሙስሊሞች ብዙ ውለታዎችን ውለዋል (አንዳንዶቹን በቅርቡ እናያቸዋለን)፡፡ ፕሮፌሰር ሃጋይ ኤልሪች ይህንን የሐሰት ትረካ የፈጠሩት ግን መልካም ስራቸውን ለማውሳት አስበው ሳይሆን “ሓጂ ዩሱፍ የንጉሡ ቀኝ እጅ ነበሩ” የሚለውን የተቃዋሚዎቻቸውን ክስ ለማጠናከር በሚል ነው፡፡

ማንም ያሻውን ይበል፡፡ ቅዱስ ቁርኣን ወደ አማርኛ የተተረጎመበት ትክክለኛው ሂደት ከላይ የገለጽኩት ነው፡፡ በእኛ በኩል በትርጉም ስራው ላይ በተሳተፉት ዑለማዎቻችን መካከል አንዳች ልዩነት አናደርግም፡፡ ሁለቱ ተርጓሚዎች፤ ሁለቱ ኤዲተሮችና ከየክፍለ ሀገሩ የተመረጡት አምስቱ አራሚዎች በሙሉ ባለውለታዎቻችን በመሆናቸው ዘወትር እናስታውሳቸዋለን፡፡ አላህ የበጎ ስራቸውን ምንዳ በጀንነት ይክፈላቸው፡፡ አሚን!!
------
አፈንዲ ሙተቂ
ታሕሳስ 22/2007
ሀረር-ምሥራቅ ኢትዮጵያ
-------
ምንጮች
1.      ቅዱስ ቁርኣን፡ የአማርኛ ትርጉም በሰይድ ሙሐመድ ሳዲቅ እና ሐጂ ሙሐመድ ሣኒ ሐቢብ፣ 1961፣ አዲስ አበባ
2.     “ቢላል መጽሔት”፡ ቅጽ 1፡ ቁጥር 9፡ ግንቦት 1985
3.     ቢላል መጽሔት፡ ቅጽ 1፡ ቁጥር 11፡ ሐምሌ 1985
4.      Patrick Desplat, The Articulation of Religious Identities and their Boundaries in Ethiopia: A Case Study on Harar, Journal of Religions in Africa, Lieden, 2005
5.     Haggai Elrich: Islam and Christianity in the Horn of Africa, Lynne Rienner Publishers, Inc, Boulder, 2010
6.    Haggai Elrich: Saudi Arabia and Ethiopia, 2003, London

------
Afendi Muteki is a researcher and author of the ethnography and history with special focus on the peoples of East Ethiopia. You may follow him on his blog and his facebook page by clicking the following links


9 comments:



  1. @@@@Thanks For Sharing..............................................................@@@@@

    Hi Your post is very attractive .very nice! Keep your post.images are super@Escort Goa
    Call Girls in Goa/
    Goa Call Girls
    Goa Escorts
    Escorts in Goaindependentgoaescorts.in/call-girls-in-goa/
    independentgoaescorts.in/goa-call-girls/
    independentgoaescorts.in/goa-escorts/
    independentgoaescorts.in/escorts-in-goa/

    Call Girls in Goa providing best Goa Escort Services.and Female Model Escorts in goa.We are offering best Call Girl services & Female Escort services in goa.For more details Contact Us:09967541580

    ReplyDelete
  2. Goa Escorts - Contact Now Miss Natasha Goa Escorts beautiful high class female escorts in Goa. High class Independent escort Girls in Goa - Call Girls Goa.


    Kolkata escorts - Kolkata Passion Avail female escort in Kolkata for the fun and pleasure. We offer best Kolkata escort girl in kolkata. Escort service in kolkata & near by areas.

    ReplyDelete
  3. Throughout the years we have constantly ensured we speak to fun, warm and alluring women at our organization.
    Escorts in Chennai

    ReplyDelete
  4. Dubai escorts are the ladies whom primary goal remains the same towards customer satisfaction.
    Dubai Tamil Escorts
    Dubai Housewife Escorts
    Dubai Independent Escorts

    ReplyDelete
  5. You won't fail to remember the amazing kind of escort services given consistently. In this way, feel free to fill your heart with joy excessively exceptional with our independent Jaipur Call Girls.

    Every one of them is very respectable, open-minded, and sizzling escorts representing rich flavors and changing over your time a great deal outstanding and mesmerising. Good gracious, definitely with hot and attractive friends, your friends will get envious. Independent Escorts Services in Jaipur Book Right Now

    Our hot Jaipur escorts will give you a warm and cozy affection. Along these lines, in the event that you are quick to go on a long outing. Quick to add some energy, at that point our hot and tasty escorts are cheerfully accessible for you in Jaipur Over here we guarantee that your vacation time is made remarkable for the duration of your life. Our hot and sizzling Jaipur Call Girls will change over your vacation time into a remarkable one. The rich and pricy flavors of hot girls will keep you electrifying all the time.

    ReplyDelete