Thursday, January 9, 2020

እውነታውን የረሳው መንግስት እና ውሉን የሳተው ተሐድሶ


ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
-----
የዶክተር አቢይ መንግስት የኢትዮጵያ ህዝቦች በከፈሉት ከባድ መስዋእነት ወደ ስልጣን ከመጣ አመት ከመንፈቅ ሆኖታል:: ይህ መንግስት በመጋቢት 2010 መጨረሻ ላይ ስልጣን ሲይዝ በርካቶች "የኢትዮጵያ ህዝቦች ለብዙ ዘመናት ሲጠይቋቸው የነበሩት ብሄራዊ የማንነት ጥያቄዎች ምላሽ የሚያገኙበትን መሠረት ይጥላል፣ የተዳከመውን የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ያነቃቃል፣ በተለያዩ ብሄሮችና ማኅበረሰቦች መካከል ብሄራዊ መግባባትን ፈጥሮ የሀገሪቷን አንድነት ከአደጋ ይታደጋል፣ በታሪካችን የመጀመሪያውን ዲሞክራሲያዊ ምርጫ የምናካሄድበት ጊዜ ደርሷል" በማለት ተስፋ ጥለውበት ነበር። ነገር ግን የሀገሪቷን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ እንኳ የማይችልና የተጀመሩትን ፕሮጀክቶች ማስፈፀም የተሳነው ደካማ መንግስት ሆኖ ተገኝቷል።

የአሁኑ መሪ ወደ ስልጣን ከመጣ ከሃያ አንድ ወር በኋላ እንኳ ራሱን ከማስተዋወቅና የራሱን ስብእና ለመገንባት ከሚሰራቸው የህዝብ ግንኙነት ስራዎች መውጣት አልቻለም። ዛሬም “መደመር” የዘመኑ በሽታችን ፍቱን መድኃኒት ነው እየተባለ ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ “ብልጽግና” የማይደፈር የማይገሰስ የዘመናት ሀብት ነው እየተባለልን ነው፡፡
---
የዚህ መንግስት ቀዳሚው ችግር እንዴት ወደ ስልጣን እንደመጣ መዘንጋቱ (ወይንም ሆን ብሎ መርሳቱ) ነው። የአሁኑ የለውጥ ሂደት የመጣው በህዝብ ትግልና መስዋእትነት ነው። ትግሉ የተጀመረው ትናንት ሳይሆን ከሃምሳ ዓመታት በፊት ነው። በዚህ ሂደትም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ውድ ህይወታቸውን ሰውተዋል።

የዶክተር አቢይ መንግስት ግን ትግሉ የዛሬ ሁለት ዓመት የተጀመረ ይመስለዋል። በትግሉ የተሳተፉትም ጠቅላይ ሚኒስትሩና ጓዶቹ ብቻ እንደሆኑ አድርጎ ደምድሟል። ለዚህም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩና ጓዶቹ በተደጋጋሚ ጊዜያት "የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችና የዲያስፖራ አክቲቪስቶች ምህረት አድርገንላቸው ወደ ሀገር እንዲገቡ ከፈቀድንላቸው በኋላ እየበጠበጡን ነው" በማለት የሚናገሩት። እኝህ ሰው ክቡር አቶ ለማ መገርሳ የኦህዴድ ሊቀመንበርነታቸውን ባይተውላቸው ኖሮ ለኢህአዴግ ሊቀመንበርነት ምርጫ የማይቀርቡ መሆናቸውን እንኳ ረስተውታል (ለማ መገርሳ ያኔ ወንበራቸውን ለቀውላቸው በአሁኑ ወቅት ከጨዋታ ውጪ ሆነዋል)

እርግጥ ጠቅላዩና ጓዶቹ የነበሩበት "ቲም ለማ" በወያኔ የመጨረሻ ዓመታት በኢህአዴግ ውስጥ ያካሄዱት ትግል ለድሉ አስተዋጽኦ ነበረው። ለዚህም እጅግ በጣም እናመሰግናቸዋለን። ነገር ግን በፓርቲው ውስጥ የፈነዳው ትግል ከፓርቲው ውጪ ሲካሄድ በነበረው ትግል ባይደገፍ ኖሮ ቲም ለማ የትም አይደርስም ነበር። ለምሳሌ የወያኔ ገዲም ጄኔራሎች አብዲ ኢሌን ቆስቁሰው በሚሊዮን የሚቆጠር ኦሮሞ ባፈናቀሉበት ወቅት ሴራውን በጥልቀት አስረድቶ ህዝቡ ከቲም ለማ ጋር እንዲቆም የቀሰቀሰው ጀዋር መሐመድ አልነበረምን? ቄሮ ቲም ለማን ደግፎ ህይወቱን ሲሰዋ አልነበረንም? ሌሎች የሀገራችን ማኅረሰቦች፣ አክቲቪስቶችና ፖለቲከኞች አብዲ ኢሌ በኦሮሞዎች ላይ ጦርነት ባወጀበት ወቅት ከኦሮሞ ወገናቸው ጋር ወግነው አልታገሉምን? አዎን! ቲም ለማ ያንን ሁሉ ድጋፍ ባያገኝ ኖሮ የፌዴራሉን ስልጣን የያዘውን ወያኔን እየተገዳደረ በትግሉ መቀጠል እንደማይችል እርግጠኛ ሆነን እንናገራለን።

የዶክተር ዐቢይ መንግስት ሁለተኛ ችግር የኢትዮጵያ ህዝቦች የሚፈልጓቸውን ነገሮች እና የታገሉላቸውን ጥያቄዎች በትክክል አለማወቁ (መዘንጋቱ) ነው። ከመሠረታዊው ነገር እንጀምርና ህዝቡ ከባድ የሆነ የኑሮ ውድነት እየጠለዘው ነው። የመሠረታዊ ሸቀጦች፣ የምግብና የአልባሳት ዋጋ በየዕለቱ እየናረ ነው። በመሆኑም ይህ መንግስት በትኩረት ሊሰራባቸው ከሚገባቸው ችግሮች አንዱ ገበያውን ማረጋጋት ሊሆን በተገባ ነበር። እርሱ ግን የሚታዩ ችግሮችን ትቶ "የከፍታ ቀን፣ መደመር፣ የመነቃቃት ቀን" እያለ የማይጨበጡ ሃሳቦችን በህዝቡ ውስጥ ለማስረጽ ሲደክም ይውላል።
በሌላ በኩል ህዝቡ በወያኔ ላይ ዱላውን ሰንዝሮ የታገለው ከዚህ ቀደም ባደረጋቸው ትግሎች የተጎናፀፋቸውን ድሎች ለማጣት እንዳልሆነ የአሁኑ መንግስት ዘንግቷል። ህዝቡ ወያኔን የታገለው ከተፈጥሮአዊ መብቶቹ መካከል ወያኔ እየሸራረፈ ያስቀራቸውን ለመጎናጸፍ እንጂ በወያኔ ዘመን የተመለሱለትን ጥያቄዎች አፈር ድሜ ለማስበላት አልነበረም።
ለምሳሌ ያህል በቅርቡ ሀገሪቱን ሊያናጋ ደርሶ የነበረውን የቋንቋ ጥያቄ እንውሰድ። ቋንቋን ማወቅ በጣም ጠቃሚ ነው። የእውቀት አማራጮችን የሚያሰፋ ፀጋ ነው። ነገር ግን ከአንድ ህዝብ የተወለዱ ልጆች የሚማሩበትን ቋንቋ መምረጥ የሚችለው ህዝቡ ራሱ ነው። ይህ ዓለም አቀፋዊ መርህ ከመሆኑም ባሻገር ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት በምትመራበት ህገ መንግስት ላይ ሰፍሯል።
የአቢይ መንግስት ግን ለዚህ ዓለም አቀፋዊ መርህ ቦታ ሳይሰጥ በእውርና ደንባራ አማካሪዎቹ እየተመራ የትምህርት ቋንቋን ሊወስንልን ተነሳ። ስድስት ወር ሙሉ "ተው" እየተባለ ቢነገረው አልሰማ አለ። ስለዚህ ህዝቡ የራሱን መብት ለማስከበር ተንቀሳቀሰ (የትምህርት ቋንቋን ለመሰወን የተሰጠው ምክንያት አስቂኝ ከመሆንም አልፎ ዘረኝነት የሚንፀባረቅበትም ነበር። "ኢትዮጵያዊነትን ለማጠናከር ሲባል ህፃናት ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ አማርኛን እንደ ተጨማሪ ቋንቋ እንዲማሩ ተወስኗል" ነበር የተባለው። ህፃናቱ በኦሮምኛ ሲማሩ ጠባብነትን ይወርሳሉ ለማለት ነው? ይገርማል!!)
ይህ በጭራሽ የህዝቡ ጥያቄ አይደለም። አልነበረምም። ቋንቋን በተመለከተ ብዙ ኦሮሞዎች ሲያነሱት የነበረው ጥያቄ "አፋን ኦሮሞ የፌዴራል መንግስቱ የስራ ቋንቋ ይሁን" የሚል ነበር። ይህንን ጥያቄ መመለስ ካልተቻለ ሌላ ነገር ሳይነካኩ ጥያቄውን ለመጪው መንግስት ማስተላለፍ ይገባ ነበር።
---
አሁን ከዋናውና እጅግ ወሳኝ ከሆነው ነጥብ ላይ ደርሰናል።
አዎን! የዚህ መንግስት ዋነኛው ችግር ከላይ የተጠቀሱትም አይደለም። የአቢይ መንግስት አቢይ ችግር በህዝብ የተመረጠ መንግስት በምርጫ እስኪተካው ድረስ ሀገሪቷን ወደ ዲሞክራሲያዊ ምዕራፍ ለማሸጋገር ሲባል ከሃይለ ማሪያም ካቢኔ ስልጣን የተረከበ የባለ አደራ መንግስት መሆኑን መዘንጋቱ ነው። ይህ መንግስት የተመረጠው በኢህአዴግ ምክር ቤት ምርጫ እንጂ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በተሳተፉበት ህዝባዊ ምርጫ አይደለም። በመሆኑም የአሁኑ መንግስት ፖሊሲና ህገ መንግስት እንዲቀይር ከየትኛውም አካል mandate አልተሰጠውም።
የዚህ በምርጫ ያልመጣው መንግስት አጣዳፊ ስራዎች መሆን የነበሩባቸው
1 ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የሚያስፈልጉ ተቋማትን መገንባት
2 የሀገሪቷን የዲሞክራሲ ጉዞ ሰንገው የያዙ ህጎችና መሻርና ማሻሻል
3 ፓርቲና መንግስትን ሙሉ በሙሉ መለያየት (ይህ ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ በድርጅት /ቤት የተመደቡ ሰዎች እንደ መንግስት ሰራተኛ ደመወዝ እየተከፈላቸው ነው። ፓርቲው በመንግስት መኪናዎች ነው የሚጠቀመው። የህወሓት፣ የኦዴፓ፣ የአዴፓ እና የደኢህዴን ቢሮዎች የሚገኙት በወረዳ አስተዳደር ጽቤቶች ውስጥ ነው። እንዲህ ዓይነቱ አሰራር ከማዕከል እስከ ወረዳ ድረስ ስሩን ሰዷል። ይህ ዐይን ያወጣ ወንጀል ነው)
4 በመንግስት ጫና የተመሠረቱ ህዝባዊ ማህበሮችን (ለምሳሌ ኦልማ፣ አልማ፣ ትልማ፣ የወጣቶች ማህበር፣ የሴቶች ማህበር ወዘተ) ከመንግስት ተፅእኖ ነፃ ማድረግ
5 የዳኝነትና የፍትሕ ስርዓቱን ከመንግስት ተፅእኖ ሙሉ በሙሉ ነፃ ማድረግ
6 የምርጫ ህጉንና የምርጫ ስርዓቱን ማሻሻል (የምርጫ ቦርዱን አባላት ከፓርቲ ንክኪ ነፃ በሆኑ ሰዎች መሙላት)
7 የጸጥታ አካላት ህጋዊነትን በተላበሰ ሁኔታ ህዝቡን እንዲያገለግሉ ማድረግ
8 ያለፉት ስርዓቶች በረጩት መርዝ ሳቢያ በተቋሰሉ ህዝቦች መካከል ትክክለኛ ሂደትን በተከተለ ሁኔታ እርቀ ሰላምን መፍጠር
9 ህዝብን ሲገድሉ፣ ሲዘርፉ፣ ሲገርፉና ሲያፈናቅሉ የኖሩ ባለስልጣናትንና የፀጥታ አካላትን ለፍርድ ማቅረብ
10 ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሁሉም ስፍራ፣ ክልል፣ ወረዳና ዞን በነፃነት የሚንቀሳቀሱበትን ሁኔታ ማመቻቸት (የተዘጉ ቢሮዎቻቸውን መክፈት፣ የታሰሩ አባላቶቻቸውን መፍታት)
11 በህዝባዊ ትግሉ ሳቢያ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን ማቋቋም (በአሁኑ ወቅት በባሌና በሀረርጌ ለረሃብና ለችግር እየተጋለጡ ነው)
12 ህገ ወጥ ታጣቂዎች በክልሎችና ድንበር አቅራቢያ በሚኖሩ ህዝቦች ላይ የሚፈፅሙትን ጥቃት ማስቆም
13 ህገ ወጥ የጦር መሳሪያና የገንዘብ ዝውውርን ማስቆም
14 ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ለሚሄደው የኑሮ ውድነት አፋጣኝ መፍትሔ ማፈላለግ
15 ወዘተ
----
ባለፈው አንድ ዓመት ከአስር ወር ጊዜ እንዳየነው ከሆነ የዶክተር አቢይ መንግስት እነዚህን ትልልቅ ተግባራት መስራቱን ዘንግቷል። ከእነርሱ ይልቅ ለጊዜያዊ ታይታና ጭብጨባ ብቻ የሚመቹ ስራዎችን ማጧጧፉን ቀጥሎበታል። ውጤቱ ግን የትም የሚያስኬድ አልሆነም። የመነቃቃትና የኩራት ቀንን ማክበር ከፌዝና ከሽሙጥ በቀር ሌላ ትርፍ የሚያስገኝ አልሆነም (ሁሉም ኢትዮጵያዊ የተደሰበት ተግባር ቢኖር የዛፍ ተከላ ዘመቻው ብቻ ነው)

ከዚህ በተቃራኒው መንግስት ለታይና ለጭብጨባ ሲል የሚፈጽማቸው ተግባራት ቀደም ሲል የተገኙ ታላላቅ ለውጦችንና ድሎችን እየቀለበሳቸው ነው። ለምሳሌ ከሁለቱ ታላላቅ ብሄሮቻችን (ኦሮሞና አማራ) በወጡ ታጋዮችና ወጣቶች መካከል ተፈጥሮ የነበረው የትግል አንድነት በዚህ ወቅት ድምጥማጡ ጠፍቷል። በነሐሴ 2010 መጀመሪያ ላይ OMN በሚሊኒየም አዳራሽ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ የተገኙት ተወዳጁ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ንግግር ሲያደርጉ ህዝቡ "ይደገም! ይደገም! ይደገም" እያለ ነበር ንግግራቸውን የተከታተለው። አሁን ግን ሁሉ ተረት ሆኖ ቀርቷል።

ወገኖቼ! እስቲ ሁለትና ሶስት ጊዜ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን እያፈረሱ ማዋቀር ምን ይባላል? የአዲስ አበባ የወንዞች ተፋሰስ ግንባታ የሚባል አቅምን ያላገናዘበ ፕሮጀክት መወጠንስ ፋይዳው ምንድነው? ለዚህ ፕሮጀክት ገንዘብ ለማሰባሰብ ተብሎ የሚሊዮን ብር የእራት ስነ ስርዓት የሚባል ከሚዲያ ፍጆታ የማያልፍ fantasy ዝግጅት ማዘጋጀትስ ትርጉሙ ምንድነው? "ኦነግን ትጥቅ ማስፈታት ቀዳሚ ስራዬ ነው" እያሉ ሽማግሌዎች ያስቀመጡትን ስትራቴጂ ሳይቀበሉ በጎኑ የጉልበተኝነት ዘዴ በማወጅ በጉዳዩ ላይ ከአንድ ዓመት በላይ መፍጀትስ? የማስተር ፕላኑ ጣጣ ሳይፈታ የኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየምን ለማከፋፈል መሞከርስ? የድንበርና የማንነት ኮሚሽን የተባለ አጨቃጫቂ መስሪያ ቤት አቋቁሞ ለንትርክ ህዝቡን መጋበዝስ? ህዝቡ ጥያቄ ሳያቀርብ “በሁሉም ትምህርት ቤቶች አማርኛ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እንደ መደበኛ ትምህርት ይሰጣል” የሚል ፍኖተ ካርታ በስራ ላይ መነሳትስ? ተቃዋሚ ፓርቲዎች ራሳቸውን ችለው በህዝቡ ውስጥ በመንቀሳቀስ መዋቅራቸውን እንዲያደራጁ እንደመደገፍ በየጊዜው ከፓርቲዎች ጋር ኮንፈረንስ መቀመጥስ? አንዳንድ ፓርቲዎችንና መሪዎቻቸውን (በተለይ ኢዜማን) ከልክ በላይ እያቀረቡና እያሞገሱ በህዝቡና በሌሎች ፓርቲዎች ዘንድ ከባድ ጥርጣሬ መፍጠርስ? ህዝቡ የዛሬ አራት ዓመት ወያኔን ወጥሮ በሚታገልበት ወቅት እንዲህ ዓይነት ጥያቄዎች ተጠይቀው ነበር?
----
ይህ መንግስት በዲፕሎማሲው ዘርፍ ጥሩ ስራ ሰርቷል። በሌላው ዘርፍ ግን በጣም የተዳከመ ነው። ከነጭራሹ ኢትዮጵያ ሰላሟን አጥታ የግጭት አውድማ ሆናለች፡፡ ለዚህ ዋነኛው ምክንያቱ ደግሞ አንድ የባለ አደራ መንግስት መስራት ያለባቸውን ዋነኛ ስራዎች መዘንጋቱ ነው። ስለዚህ ወደ መነሻው ተመልሶ በተቀሩት ወራት ውጤታማ ስራ እንዲሰራ በአክብሮት እንጠይቃለን።

ህዝቡና አክቲቪስቱ እየተፈጠረ ላለው ችግር እንደ ምክንያት ሲጠቀሱ እናያለን። ለህዝባቸው የታገሉት ወጣቶች ጣት እየተጠቆመባቸው "መንጋውና ጎረምሳው ስራ አላሰራ አለ" እየተባሉ ይወቀሳሉ። እርግጥ በወጣቶቻችን ዘንድ አለመስከን እና ችኮላ ይታያል። ነገር ግን ዋናው የችግሩ ምንጭ ወጣቱን ከጎኑ አሰልፎ ለውጡን ማሻገር ያቃተው መንግስት ነው እንጂ ሌላ አካል አይደለም። ይህ ለህዝቡና ለሀገሩ ለውጥ ለማምጣት ሲል የሞተው ወጣት ዛሬም ስራ አጥ ነው። መንግስት ተብዬው ደግሞ ለወጣቱ ስራ መፍጠርን ትቶ በየእለቱና በየሳምንቱ "የምንትስ ቀን አከብራለሁ" እያለ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ይረጫል። “የመደመር መጽሐፍ ለኢትዮጵያ ፍቱን መድኃኒት ነው” በማለት በእርሱ ላይ ብዙ ብር አውጥቶ ህዝቡን ያሸብራል፡፡ የሚያደንቁትንና እርሱ የሚወዳቸውን አይነት ግጥም የሚያነቡለትን አሸርጋጆች በሸራተንና በቤተ መንግስት እየጋበዘ ራሱን ያሽሞነሙናል። ዘይገርም!!
-----
ሀገሪቱን የምትመሩ ሰዎች ሆይ!

ለምርጫው አራት ወር ብቻ ይቀራል፡፡ እናንተም በህጋዊ መንገድ ሀገሪቱን መምራት የምትችሉት ለአራት ወራት ብቻ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ህዝቡ ለመረጠው መንግሥት ስልጣን ማስረከብ ይኖርባችኋል፡፡ የራሳችሁን ግለ-ስብእና ስትገነቡ እና በአዳዲስ ሃሳቦች ስትደነጋገሩ ጊዜው እያለቀ ነው፡፡ አሁንም ወደ ህሊናችሁ ተመልሳችሁ ሀገሪቱን ከጥፋት እንድትታደጓት ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
-----
አፈንዲ ሙተቂ
መስከረም 1/2012

Sunday, January 5, 2020

Two Days in Brief: A Stay with Atoomsa Kumsaa of OLF


Written by: Afendi Muteki
---



I know the man pictured with me on this photo 28 years ago. His name is Atoomsa Kumsaa. I saw Atoomsaa for the first time in December 1991 when the Oromo Liberation Front (OLF) organized a festival that marked the resurrection of the congress of the “caffee gadaa” assembly of Odaa Bultum which was banned for more than 100 years under the successive Ethiopian regimes.


Atoomsaa Kumsaa was one of the leaders of OLF in early 1990s. That was the reason for which he fall in to the sight of mine and many others when he came to Odaa Bultum in December 1991. After the completion of the celebration of the feast of Odaa Bultum, I continued to see him occasionally as when he comes to Galamso, my hometown, to carry out the tasks of his organization.


After OLF quitted the transitional government of Ethiopia in June 1992 under the pressures of EPRDF and started the armed struggle, however, I haven’t seen Atoomsaa for a single day. I never heard of him, neither did I read about him in the press. Due to the unavailability of information on his whereabouts, I closely came to a conclusion that he might had been martyred in one of the bloody battles fought between OLF and EPRDF in Eastern Oromia in 1992-1998.


Those intensive battles and the war fought between OLF and EPRDF in other parts of Oromia (Wallaga, Bale, Borana, western Shawa etc) are largely untold. Their history is rarely written. The media gave them little attention. But the Oromo public at large still remember that the lives of many members of OLA and their brilliant commanders were lost in the war. Political leaders of OLF like Nadhii Gammadaa, Buruysoo Boruu, Bilal Waaqayyo, Jiraa Leencoo etc were martyred in those battles; gallant OLA commanders including Hambisaa Soolee, Daddafaa Dhaqqabaa, Yaadataa Bariisoo, Arbii Miillii, Waarituu Waare etc fought bravely the aggressors and died for the national rights and the liberty of the Oromo people in those years.


As the Oromo martyrs of that remarkable era amount to tens of thousands, it was natural to assume that Atoomsaa might have been martyred in one of those battles. When I saw him recently in my hometown, however, I felt unconditional joy and screamed as if my dead brother were resurrected from his grave. I tried to rehearse my memory again and again and realized that it was not a dream. And having undertaken certain rudimentary checkups, I proved that I am not mistaken with another guy.


It is the same Atoomsaa Kumsaa that I knew in 1991-1992. It is that Atoomsaa to whom the people of Eastern Oromia gave much applaud for his guerrilla tactics and bravery. It is Atoomsa Kumsaa whom we were calling “Ramboo Part III” for his charisma, grace and fighting abilities
----
Atoomsaa Kumsaa was one of the brilliant commanders OLA (Oromo Liberation Army) had ever seen in its long armed struggle. He was the commander-in-chief of the eastern division of OLA in 1991-1997 (note: OLA had three divisions then; they were called the eastern, the south eastern and the western divisions. Atoomsaa was the commander of the eastern division, Abbaa Caalaa Lataa was the commander of the western division and Guutama Hawaas was the commander of the south eastern division).


During that time Atoomsa’s main sit was the town Dadar in East Hararge zone. But as he was assigned to lead the largest division of OLA that spread from Dhummugaa in Arsi to Jjjiga in the tip of Eastern Hararge, he used to visit the towns of the whole Hararge region. Mostly importantly he was seen in Galamso since it was serving as OLF’s defacto capital for West Harerghe and Arsi zones. That was the reason for which I encountered him in my hometown multiple times.
----
Atoomsaa’s history of participation in the Oromo people’s struggle starts from his early age. He was born in Haramaya, East Hararge, a town revered as a home of famous Oromo nationalists and important public uprisings. In his hometown, he participated in the clandestine groups which were founded to galvanize the Oromo freedom struggle in the area. When the military government of Ethiopia (i.e. the Dergue regime) waged a brutal campaign to silence the Oromo liberation struggle in all provinces of Oromia, he went to the jungles of Garamulata and joined OLF.


Up on his arrival at the OLA camp, Atoomsaa was made a member of the “Aayidaa”, a division of very young OLA combatants. As his age progressed, he served the organization and the Oromo people in different positions, from a single combatant up to a member of the supreme executive council of OLF. And when I knew him in 1991, he was a member of the Politburo of OLF and the commander in chief of OLA’s East Oromia division.


According to multiple sources, Atoomsaa Kumsaa was one of the chief architects of the military operations OLA undertook in eastern Oromia in 1980s and 1990s. He was a tactician of guerrilla warfare and a planer of many attacks that the Oromo freedom fighters waged against the Dergue and the EPRDF regimes. When OLF was a member of the transitional government (from June 1991-June 1992), Atoomsaa served as a member of the joint committee founded by OLF and EPRDF to avert a clash between the armies of the two organizations. He was also a member of the committee formed by the governments of Eritrea and USA in order to encamp the armies of OLF and EPRDF and make necessary arrangements for the highly anticipated election of 1992.


Following OLF’s withdrawal from the transitional government in June 1992, he resumed his command of OLA’s military operations in the highlands and lowlands of eastern Oromia. He and the notable leaders of OLA in his area of command such as Daddafaa Dhaqqabaa, Yaadataa Bariisoo, Leencoo Elemoo, Hambisaa Soolee, Aaneessoo Waaree, Waarituu Waaree, Raggaatuu Roobaa, Muraad Haashim, Caccabsaa Odaa, Ahmad Leemman, Gootomsaa Daadhii, Dayyaas Daadhii, Tokkumaa Sabaa, Duumeessoo Waariyoo and others, together with thousands of Oromo youth, fought selflessly the highly equipped and savage army of EPRDF for days and nights.


Atoomsaa was also highly admired by the members of OLA and the OLF’s political leaders who passed many years in the eastern front (Galaasaa Dilboo, Nadhii Gammadaa, Buruuysoo Boruu, Dhugaasaa Bakakkoo, Dhugoomsaa Dhugaasaa, Tujii Raggaasaa, Bobbaasaa Gadaa etc) for his organizational skills, humbleness, commitment and punctuality. His combat skills were praised both by his enemies and his friends. EPRDF designed many plans to kill him smoothly but failed. He was ambushed by rocket launchers and military helicopters repeatedly but escaped those skillfully planned operations. After many years of ups and downs, and the tremendous hardships of the long term Oromo people’s liberation struggle, he survived as one of the main veterans of Oromo Liberation Front.
----
I passed two days with Atoomsaa Kumsaa in my hometown (Galamso) and I observed that his fluency and eloquence are still intact. His skill to clarify the ambiguous issues and topics raised by my friends is so amazing. He told us that currently he is a member of the supreme executive council of OLF and a head of the social affairs committee of the organization. But the name in which he addressed the organization’s supreme council is different from the one I know before 28 years.


Atoomsaa said “I am a member of Gumii Shanee of OLF”. I inquired “What is this Gumii Shanee? A new organization? And you were a member of the Politburo of OLF in 1992. So are you demoted or promoted?”
Atoomsaa smiled and replied “Politburo and Gumii Shanee are the same. The former Politburo was renamed "Gumii Shanee" following the tradition of the Oromo of Borana who call their executive council of their Gadaa assembly “Gumii Shanee”. It was renamed so on the OLF’s Mogadishu Congress of 1999. The organization made this change learning that the name “Politburo”, which implies a socialist orientation but which we left a long time ago, wasn’t comfortable to many members. So the old name “Politburo” was replaced by the new “Gumii Shanee”. No change was made on the name of the organization, and there is no organization called “Shanee” for sure. This name refers to only the executive council of our organization”
----
My two days stay with Atoomsaa Kumsaa were very amusing and fruitful. His encyclopedic knowledge of the history of the Oromo liberation struggle in general and that of OLF in particular made me to plan writing a full book in which he will be read as a central figure. Meet me when we have the book.
----
Afendi Muteki
January 5/2020
Galamso, West Hararge